1ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ።
1And Jesus answering spoke to them again in parables, saying,
2መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች።
2The kingdom of the heavens has become like a king who made a wedding feast for his son,
3የታደሙትንም ወደ ሰርጉ ይጠሩ ዘንድ ባሮቹን ላከ ሊመጡም አልወደዱም።
3and sent his bondmen to call the persons invited to the wedding feast, and they would not come.
4ደግሞ ሌሎችን ባሮች ልኮ። የታደሙትን። እነሆ፥ ድግሴን አዘጋጀሁ፥ ኮርማዎቼና የሰቡት ከብቶቼ ታርደዋል፥ ሁሉም ተዘጋጅቶአል፤ ወደ ሰርጉ ኑ በሉአቸው አለ።
4Again he sent other bondmen, saying, Say to the persons invited, Behold, I have prepared my dinner; my oxen and my fatted beasts are killed, and all things ready; come to the wedding feast.
5እነርሱ ግን ቸል ብለው አንዱ ወደ እርሻው፥ ሌላውም ወደ ንግዱ ሄደ፤
5But they made light of it, and went, one to his own land, and another to his commerce.
6የቀሩትም ባሮቹን ይዘው አንገላቱአቸው ገደሉአቸውም።
6And the rest, laying hold of his bondmen, ill-treated and slew [them].
7ንጉሡም ተቈጣ፥ ጭፍሮቹንም ልኮ እነዚያን ገዳዮች አጠፋ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ።
7And [when] the king [heard of it he] was wroth, and having sent his forces, destroyed those murderers and burned their city.
8በዚያን ጊዜ ባሮቹን። ሰርጉስ ተዘጋጅቶአል፥ ነገር ግን የታደሙት የማይገባቸው ሆኑ፤
8Then he says to his bondmen, The wedding feast is ready, but those invited were not worthy;
9እንግዲህ ወደ መንገድ መተላለፊያ ሄዳችሁ ያገኛችሁትን ሁሉ ወደ ሰርጉ ጥሩ አለ።
9go therefore into the thoroughfares of the highways, and as many as ye shall find invite to the wedding feast.
10እነዚያም ባሮች ወደ መንገድ ወጥተው ያገኙትን ሁሉ ክፉዎችንም በጎዎችንም ሰበሰቡ፤ የሰርጉንም ቤት ተቀማጮች ሞሉት።
10And those bondmen went out into the highways, and brought together all as many as they found, both evil and good; and the wedding feast was furnished with guests.
11ንጉሡም የተቀመጡትን ለማየት በገባ ጊዜ በዚያ የሰርግ ልብስ ያለበሰ አንድ ሰው አየና። ወዳጄ ሆይ፥
11And the king, having gone in to see the guests, beheld there a man not clothed with a wedding garment.
12የሰርግ ልብስ ሳትለብስ እንዴት ወደዚህ ገባህ? አለው እርሱም ዝም አለ።
12And he says to him, [My] friend, how camest thou in here not having on a wedding garment? But he was speechless.
13በዚያን ጊዜ ንጉሡ አገልጋዮቹን። እጁንና እግሩን አስራችሁ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል አለ።
13Then said the king to the servants, Bind him feet and hands, and take him away, and cast him out into the outer darkness: there shall be the weeping and the gnashing of teeth.
14የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።
14For many are called ones, but few chosen ones.
15ስለዚህ ፈሪሳውያን ሄዱና እንዴት አድርገው በነገር እንዲያጠምዱት ተማከሩ።
15Then went the Pharisees and held a council how they might ensnare him in speaking.
16ደቀ መዛሙርታቸውንም ከሄሮድስ ወገን ጋር ላኩበት፥ እነርሱም። መምህር ሆይ፥ እውነተኛ እንደ ሆንህ በእውነትም የእግዚአብሔርን መንገድ እንድታስተምር እናውቃለን፥ ለማንምም አታደላም፥ የሰውን ፊት አትመለከትምና፤
16And they send out to him their disciples with the Herodians, saying, Teacher, we know that thou art true and teachest the way of God in truth, and carest not for any one, for thou regardest not men's person;
17እንግዲህ ምን ይመስልሃል? ንገረን ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? አሉት።
17tell us therefore what thou thinkest: Is it lawful to give tribute to Caesar, or not?
18ኢየሱስም ክፋታቸውን አውቆ። እናንተ ግብዞች፥ ስለ ምን ትፈትኑኛላችሁ?
18But Jesus, knowing their wickedness, said, Why tempt ye me, hypocrites?
19የግብሩን ብር አሳዩኝ አለ። እነርሱም ዲናር አመጡለት።
19Shew me the money of the tribute. And they presented to him a denarius.
20እርሱም። ይህች መልክ ጽሕፈቲቱስ የማን ናት? አላቸው።
20And he says to them, Whose [is] this image and superscription?
21የቄሣር ነው አሉት። በዚያን ጊዜ። እንኪያስ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ አላቸው።
21They say to him, Caesar's. Then he says to them, Pay then what is Caesar's to Caesar, and what is God's to God.
22ይህንም ሰምተው ተደነቁ፥ ትተውትም ሄዱ።
22And when they heard [him], they wondered, and left him, and went away.
23በዚያን ቀን። ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ ቀረቡ፥
23On that day came to him Sadducees, who say there is no resurrection; and they demanded of him,
24እንዲህም ብለው ጠየቁት። መምህር ሆይ፥ ሙሴ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሲሞት ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካ አለ።
24saying, Teacher, Moses said, If any one die, not having children, his brother shall marry his wife and shall raise up seed to his brother.
25ሰባት ወንድማማች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ፥ ዘርም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት፤
25Now there were with us seven brethren; and the first having married died, and not having seed, left his wife to his brother.
26እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው ሦስተኛውም፥ እስከ ሰባተኛው ድረስ።
26In like manner also the second and the third, unto the seven.
27ከሁሉም በኋላ ሴቲቱ ሞተች።
27And last of all the woman also died.
28ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀንስ፥ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች?
28In the resurrection therefore of which of the seven shall she be wife, for all had her?
29ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።
29And Jesus answering said to them, Ye err, not knowing the scriptures nor the power of God.
30በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም።
30For in the resurrection they neither marry nor are given in marriage, but are as angels of God in heaven.
31ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን። እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።
31But concerning the resurrection of the dead, have ye not read what was spoken to you by God, saying,
33ሕዝቡም ይህን ሰምተው በትምህርቱ ተገረሙ።
32*I* am the God of Abraham, and the God of Isaac, and the God of Jacob? God is not God of [the] dead, but of [the] living.
34ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ዝም እንዳሰኛቸው በሰሙ ጊዜ አብረው ተሰበሰቡ።
33And when the crowds heard [it] they were astonished at his doctrine.
35ከእነርሱም አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው።
34But the Pharisees, having heard that he had put the Sadducees to silence, were gathered together.
36መምህር ሆይ፥ ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ብሎ ጠየቀው።
35And one of them, a lawyer, demanded, tempting him, and saying,
37ኢየሱስም እንዲህ አለው። ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ።
36Teacher, which is the great commandment in the law?
38ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
37And he said to him, Thou shalt love [the] Lord thy God with all thy heart, and with all thy soul, and with all thy understanding.
39ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም። ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት።
38This is [the] great and first commandment.
40በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።
39And [the] second is like it, Thou shalt love thy neighbour as thyself.
41ፈሪሳውያንም ተሰብስበው ሳሉ፥ ኢየሱስ። ስለ ክርስቶስ ምን ይመስላችኋል? የማንስ ልጅ ነው? ብሎ ጠየቃቸው። የዳዊት ልጅ ነው አሉት።
40On these two commandments the whole law and the prophets hang.
43እርሱም። እንኪያስ ዳዊት። ጌታ ጌታዬን። ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው ሲል እንዴት በመንፈስ ጌታ ብሎ ይጠራዋል?
41And the Pharisees being gathered together, Jesus demanded of them,
45ዳዊትስ ጌታ ብሎ ከጠራው፥ እንዴት ልጁ ይሆናል? አላቸው።
42saying, What think ye concerning the Christ? whose son is he? They say to him, David's.
46አንድም ቃል ስንኳ ይመልስለት ዘንድ የተቻለው የለም፥ ከዚያ ቀንም ጀምሮ ወደ ፊት ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም።
43He says to them, How then does David in Spirit call him Lord, saying,
44The Lord said to my Lord, Sit on my right hand until I put thine enemies under thy feet?
45If therefore David call him Lord, how is he his son?
46And no one was able to answer him a word, nor did any one dare from that day to question him any more.