1በዚያም ወራት ዓለሙ ሁሉ እንዲጻፍ ከአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ ወጣች።
1Now it happened in those days, that a decree went out from Caesar Augustus that all the world should be enrolled.
2ቄሬኔዎስ በሶርያ አገር ገዥ በነበረ ጊዜ ይህ የመጀመሪያ ጽሕፈት ሆነ።
2This was the first enrollment made when Quirinius was governor of Syria.
3ሁሉም እያንዳንዱ ይጻፍ ዘንድ ወደ ከተማው ሄደ።
3All went to enroll themselves, everyone to his own city.
4ዮሴፍም ደግሞ ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ ከገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ ቤተ ልሔም ወደምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ይሁዳ፥ ፀንሳ ከነበረች ከእጮኛው ከማርያም ጋር ይጻፍ ዘንድ ወጣ።
4Joseph also went up from Galilee, out of the city of Nazareth, into Judea, to the city of David, which is called Bethlehem, because he was of the house and family of David;
6በዚያም ሳሉ የመውለጃዋ ወራት ደረሰ፥
5to enroll himself with Mary, who was pledged to be married to him as wife, being pregnant.
7የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው።
6It happened, while they were there, that the day had come that she should give birth.
8በዚያም ምድር መንጋቸውን በሌሊት ሲጠብቁ በሜዳ ያደሩ እረኞች ነበሩ።
7She brought forth her firstborn son, and she wrapped him in bands of cloth, and laid him in a feeding trough, because there was no room for them in the inn.
9እነሆም፥ የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ።
8There were shepherds in the same country staying in the field, and keeping watch by night over their flock.
10መልአኩም እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤
9Behold, an angel of the Lord stood by them, and the glory of the Lord shone around them, and they were terrified.
11ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።
10The angel said to them, “Don’t be afraid, for behold, I bring you good news of great joy which will be to all the people.
12ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ።
11For there is born to you, this day, in the city of David, a Savior, who is Christ the Lord.
13ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ።
12This is the sign to you: you will find a baby wrapped in strips of cloth, lying in a feeding trough.”
14ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።
13Suddenly, there was with the angel a multitude of the heavenly army praising God, and saying,
15መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ፥ እረኞቹ እርስ በርሳቸው። እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ ተባባሉ።
14“Glory to God in the highest, on earth peace, good will toward men.”
16ፈጥነውም መጡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ።
15It happened, when the angels went away from them into the sky, that the shepherds said one to another, “Let’s go to Bethlehem, now, and see this thing that has happened, which the Lord has made known to us.”
17አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ።
16They came with haste, and found both Mary and Joseph, and the baby was lying in the feeding trough.
18የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሩአቸው ነገር አደነቁ፤
17When they saw it, they publicized widely the saying which was spoken to them about this child.
19ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር።
18All who heard it wondered at the things which were spoken to them by the shepherds.
20እረኞችም እንደ ተባለላቸው ስለ ሰሙትና ስላዩት ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያከበሩ ተመለሱ።
19But Mary kept all these sayings, pondering them in her heart.
21ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ።
20The shepherds returned, glorifying and praising God for all the things that they had heard and seen, just as it was told them.
22እንደ ሙሴም ሕግ የመንጻታቸው ወራት በተፈጸመ ጊዜ፥ በጌታ ሕግ። የእናቱን ማኅፀን የሚከፍት ወንድ ሁሉ ለጌታ የተቀደሰ ይባላል ተብሎ እንደ ተጻፈ በጌታ ፊት ሊያቆሙት፥ በጌታም ሕግ። ሁለት ዋሊያ ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች እንደ ተባለ፥ መሥዋዕት ሊያቀርቡ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት።
21When eight days were fulfilled for the circumcision of the child, his name was called Jesus, which was given by the angel before he was conceived in the womb.
25እነሆም፥ በኢየሩሳሌም ስምዖን የሚባል ሰው ነበረ፥ ይህም ሰው የእስራኤልን መጽናናት ይጠባበቅ ነበር፤ ጻድቅና ትጉህም ነበረ፥ መንፈስ ቅዱስም በእርሱ ላይ ነበረ።
22When the days of their purification according to the law of Moses were fulfilled, they brought him up to Jerusalem, to present him to the Lord
26በጌታም የተቀባውን ሳያይ ሞትን እንዳያይ በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ ነበር።
23(as it is written in the law of the Lord, “Every male who opens the womb shall be called holy to the Lord”), Exodus 13:2,12
27በመንፈስም ወደ መቅደስ ወጣ፤ ወላጆቹም እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕፃኑን ኢየሱስን በአስገቡት ጊዜ፥
24and to offer a sacrifice according to that which is said in the law of the Lord, “A pair of turtledoves, or two young pigeons.” Leviticus 12:8
28እርሱ ደግሞ ተቀብሎ አቀፈው እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ።
25Behold, there was a man in Jerusalem whose name was Simeon. This man was righteous and devout, looking for the consolation of Israel, and the Holy Spirit was on him.
29ጌታ ሆይ፥ አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤
26It had been revealed to him by the Holy Spirit that he should not see death before he had seen the Lord’s Christ. “Christ” (Greek) and “Messiah” (Hebrew) both mean “Anointed One”
30ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና፤
27He came in the Spirit into the temple. When the parents brought in the child, Jesus, that they might do concerning him according to the custom of the law,
32ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን ለሕዝብህም ለእስራኤል ክብር ነው።
28then he received him into his arms, and blessed God, and said,
33ዮሴፍና እናቱም ስለ እርሱ በተባለው ነገር ይደነቁ ነበር።
29“Now you are releasing your servant, Master, according to your word, in peace;
34ስምዖንም ባረካቸው እናቱን ማርያምንም። እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት።
30for my eyes have seen your salvation,
36ከአሴር ወገንም የምትሆን የፋኑኤል ልጅ ሐና የምትባል አንዲት ነቢይት ነበረች፤ እርስዋም ከድንግልናዋ ጀምራ ከባልዋ ጋር ሰባት ዓመት ኖረች፤
31which you have prepared before the face of all peoples;
37እርስዋም ሰማኒያ አራት ዓመት ያህል መበለት ሆና በጣም አርጅታ ነበር፤ በጾምና በጸሎትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር።
32a light for revelation to the nations, and the glory of your people Israel.”
38በዚያችም ሰዓት ቀርባ እግዚአብሔርን አመሰገነች፤ የኢየሩሳሌምንም ቤዛ ለሚጠባበቁ ሁሉ ስለ እርሱ ትናገር ነበር።
33Joseph and his mother were marveling at the things which were spoken concerning him,
39ሁሉንም እንደ ጌታ ሕግ ከፈጸሙ በኋላ፥ ወደ ገሊላ ወደ ከተማቸው ወደ ናዝሬት ተመለሱ።
34and Simeon blessed them, and said to Mary, his mother, “Behold, this child is set for the falling and the rising of many in Israel, and for a sign which is spoken against.
40ሕፃኑም አደገ፥ ጥበብም ሞልቶበት በመንፈስ ጠነከረ፤ የእግዚአብሔርም ጸጋ በእርሱ ላይ ነበረ።
35Yes, a sword will pierce through your own soul, that the thoughts of many hearts may be revealed.”
41ወላጆቹም በያመቱ በፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ነበር።
36There was one Anna, a prophetess, the daughter of Phanuel, of the tribe of Asher (she was of a great age, having lived with a husband seven years from her virginity,
42የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤
37and she had been a widow for about eighty-four years), who didn’t depart from the temple, worshipping with fastings and petitions night and day.
43ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር።
38Coming up at that very hour, she gave thanks to the Lord, and spoke of him to all those who were looking for redemption in Jerusalem.
44ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለ መሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤
39When they had accomplished all things that were according to the law of the Lord, they returned into Galilee, to their own city, Nazareth.
45ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።
40The child was growing, and was becoming strong in spirit, being filled with wisdom, and the grace of God was upon him.
46ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤
41His parents went every year to Jerusalem at the feast of the Passover.
47የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ።
42When he was twelve years old, they went up to Jerusalem according to the custom of the feast,
48ባዩትም ጊዜ ተገረሙ፥ እናቱም። ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው።
43and when they had fulfilled the days, as they were returning, the boy Jesus stayed behind in Jerusalem. Joseph and his mother didn’t know it,
49እርሱም። ስለ ምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው።
44but supposing him to be in the company, they went a day’s journey, and they looked for him among their relatives and acquaintances.
50እነርሱም የተናገራቸውን ነገር አላስተዋሉም።
45When they didn’t find him, they returned to Jerusalem, looking for him.
51ከእነርሱም ጋር ወርዶ ወደ ናዝሬት መጣ፥ ይታዘዝላቸውም ነበር። እናቱም ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ ትጠብቀው ነበር።
46It happened after three days they found him in the temple, sitting in the midst of the teachers, both listening to them, and asking them questions.
52ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።
47All who heard him were amazed at his understanding and his answers.
48When they saw him, they were astonished, and his mother said to him, “Son, why have you treated us this way? Behold, your father and I were anxiously looking for you.”
49He said to them, “Why were you looking for me? Didn’t you know that I must be in my Father’s house?”
50They didn’t understand the saying which he spoke to them.
51And he went down with them, and came to Nazareth. He was subject to them, and his mother kept all these sayings in her heart.
52And Jesus increased in wisdom and stature, and in favor with God and men.