Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

1 Corinthians

14

1Tiecieties pēc mīlestības, pūlieties pēc garīgajām dāvanām, bet sevišķi, lai jums būtu praviešu dāvanas!
1ፍቅርን ተከታተሉ፥ መንፈሳዊ ስጦታንም ይልቁንም ትንቢት መናገርን በብርቱ ፈልጉ።
2Jo kas runā valodās, tas nerunā cilvēkiem, bet Dievam, jo neviens to nesaprot; bet garā viņš runā noslēpumus.
2በልሳን የሚናገርስ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርም፤ የሚያስተውለው የለምና፥ በመንፈስ ግን ምሥጢርን ይናገራል፤
3Bet kas pravieto, tas runā cilvēku celšanai, paskubināšanai un iepriecināšanai.
3ትንቢትን የሚናገር ግን ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ለሰው ይናገራል።
4Kas runā valodās, tas paceļ pats sevi, bet kas pravieto, tas ceļ Dieva Baznīcu.
4በልሳን የሚናገር ራሱን ያንጻል፤ ትንቢትን የሚናገር ግን ማኅበሩን ያንጻል።
5Bet es vēlos, ka jūs visi runātu valodās, bet vēl vairāk, lai jūs pravietotu; jo lielāks ir tas, kas pravieto, nekā tas, kas runā valodās, ja viņš to nepaskaidro, lai draudze tiktu stiprināta.
5ሁላችሁ በልሳኖች ልትናገሩ እወድ ነበር፥ ትንቢትን ልትናገሩ ግን ከዚህ ይልቅ እወዳለሁ፤ ማኅበሩ ይታነጽ ዘንድ ንግግሩን ባይተረጐም በልሳኖች ከሚናገር ትንቢትን የሚናገር ይበልጣል።
6Bet, brāļi, ja es tagad nāktu pie jums un runātu valodās, ko tas jums līdzētu, ja es nesludinātu jums vai nu atklāsmi, vai zināšanas, vai pravietojumus, vai mācību?
6አሁን ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ወደ እናንተ መጥቼ በልሳኖች ብናገር፥ በመግለጥ ወይም በእውቀት ወይም በትንቢት ወይም በትምህርት ካልነገርኋችሁ ምን እጠቅማችኋለሁ?
7Tas tāpat kā ar nedzīviem priekšmetiem, kas rada skaņas, vai tā būtu stabule, vai kokle; ja tās neskanētu dažādi, kā tad būtu izšķirams, kā skan stabule un kā skan kokle?
7ነፍስ የሌለበት ነገር እንኳ ዋሽንትም ክራርም ቢሆን ድምፅ ሲሰጥ የድምፁን ልዩነት ባይገልጥ በዋሽንት የሚነፋው ወይስ በክራር የሚመታው መዝሙር እንዴት ይታወቃል?
8Un ja taure dos nenoteiktu skaņu, kas tad gatavosies karam?
8ደግሞም መለከት የማይገለጥን ድምፅ ቢሰጥ ለጦርነት ማን ይዘጋጃል?
9Tā arī jūs valodas ziņā. Ja jūs nerunāsiet skaidru valodu, kā lai saprot to, kas tiek runāts? Jūs runāsiet vējam.
9እንዲሁ እናንተ ደግሞ የተገለጠውን ቃል በአንደበት ባትናገሩ ሰዎች የምትናገሩትን እንዴት አድርገው ያስተውሉታል? ለነፋስ የምትናገሩ ትሆናላችሁና።
10Šinī pasaulē ir tik daudz dažādu valodu, un bez skaņas nav nekā.
10በዓለም ምናልባት ቁጥር የሌለው የቋንቋ ዓይነት ይኖራል ቋንቋም የሌለው ሕዝብ የለም፤
11Un ja es vārdu nozīmi nesaprotu, tad es esmu svešinieks tam, kam runāju, un tas, kas runā, ir man svešinieks.
11እንግዲህ የቋንቋውን ፍች ባላውቅ ለሚናገረው እንግዳ እሆናለሁ፥ የሚናገረውም ለእኔ እንግዳ ይሆናል።
12Tā arī jūs, cenzdamies pēc gara dāvanam, rūpējieties, lai jūs būtu bagāti ar tām draudzes celšanai!
12እንዲሁ ደግሞ እናንተ መንፈሳዊ ስጦታን በብርቱ የምትፈልጉ ከሆናችሁ ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ እንዲበዛላችሁ ፈልጉ።
13Tādēļ, kas runā valodās, lai lūdz Dievu, ka var to izskaidrot.
13ስለዚህ በልሳን የሚናገር እንዲተረጉም ይጸልይ።
14Ja es kādā valodā lūdzu Dievu, tad mans gars gan pielūdz Dievu, bet mans prāts paliek bez augļiem.
14በልሳን ብጸልይ መንፈሴ ይጸልያል አእምሮዬ ግን ያለ ፍሬ ነው።
15Kas tad iznāk? Es gribu lūgt Dievu garā, es gribu lūgt Dievu arī ar prātu; es gribu dziedāt garā, es gribu dziedāt arī ar prātu.
15እንግዲህ ምንድር ነው? በመንፈስ እጸልያለሁ በአእምሮም ደግሞ እጸልያለሁ፤ በመንፈስ እዘምራለሁ በአእምሮም ደግሞ እዘምራለሁ።
16Bez tam, ja tu garā godināsi Dievu, kā tad vienkāršais cilvēks varēs pateikt "amen" tavai Dieva godināšanai, ja viņš nesaprot to, ko tu saki?
16እንዲያማ ካልሆነ፥ አንተ በመንፈስ ብትባርክ ባልተማሩት ስፍራ የተቀመጠው የምትለውን ካላወቀ እንዴት አድርጎ ለምስጋናህ አሜን ይላል?
17Jo tava pateicība ir gan laba, bet cits netiek ar to pacelts.
17አንተማ መልካም ታመሰግናለህ፥ ሌላው ግን አይታነጽበትም።
18Es pateicos savam Dievam, ka es runāju visās jūsu valodās.
18ከሁላችሁ ይልቅ በልሳኖች እናገራለሁና እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤
19Bet draudzē es labāk gribu pateikt piecus vārdus ar savu saprašanu, lai arī citus pamācītu, nekā desmit tūkstošu vārdu valodās.
19ነገር ግን ሌሎችን ደግሞ አስተምር ዘንድ በማኅበር እልፍ ቃላት በልሳን ከመናገር ይልቅ አምስት ቃላት በአእምሮዬ ልናገር እወዳለሁ።
20Brāļi, netopiet bērni saprašanā, bet ļaunuma ziņā esiet bērni! Saprašanā esiet pilnīgi!
20ወንድሞች ሆይ፥ በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ፤ ለክፋት ነገር ሕፃናት ሁኑ እንጂ በአእምሮ የበሰሉ ሁኑ።
21Likumā ir rakstīts: Svešās valodās un svešām lūpām es runāšu šai tautai, un arī tad viņa mani neklausīs, saka Kungs. (Is.28,11)
21ሌሎችን ልሳኖች በሚናገሩ ሰዎችና በሌላ አንደበት ለዚህ ሕዝብ እነግራቸዋለሁ፥ እንዲህም ቢሆን አይሰሙኝም ይላል ጌታ ተብሎ በሕግ ተጽፎአል።
22Tāpēc valodas ir zīme nevis ticīgajiem, bet neticīgajiem, bet pravietojumi nav neticīgajiem, bet ticīgajiem.
22እንግዲያስ በልሳኖች መናገር ለማያምኑ ምልክት ነው እንጂ ለሚያምኑ አይደለም፥ ትንቢት ግን ለሚያምኑ እንጂ ለማያምኑ አይደለም።
23Ja visa Baznīca sanāktu kopā, un visi runātu valodās, bet ienāktu arī nepratēji vai neticīgie, vai tad tie nepateiks, ka jūs esat ārprātīgi?
23እንግዲህ ማኅበር ሁሉ አብረው ቢሰበሰቡ ሁሉም በልሳኖች ቢናገሩና ያልተማሩ ወይም የማያምኑ ሰዎች ቢገቡ። አብደዋል አይሉምን?
24Bet ja, visiem pravietojot, ienāktu neticīgais vai nepratējs, un visi viņu pārliecinātu, visi viņu pārbaudītu,
24ሁሉ ትንቢት ቢናገሩ ግን የማያምን ወይም ያልተማረ ሰው ቢገባ በሁሉ ይወቀሳል፥ በሁሉም ይመረመራል፤
25Viņa sirds noslēpumi tiktu atklāti, tad viņš, uz sava vaiga nokritis, pielūgs Dievu un pasludinās, ka jūsos patiesi ir Dievs.
25በልቡም የተሰወረ ይገለጣል እንዲሁም። እግዚአብሔር በእውነት በመካከላቸው ነው ብሎ እየተናገረ በፊቱ ወድቆ ለእግዚአብሔር ይሰግዳል።
26Ko tad darīt, brāļi? Kad jūs sapulcējaties, tad katram no jums ir psalms vai mācība, vai izskaidrojumi, tas viss lai notiek pacelšanai!
26እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ምንድር ነው? በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለእያንዳንዱ መዝሙር አለው፥ ትምህርት አለው፥ መግለጥ አለው፥ በልሳን መናገር አለው፥ መተርጐም አለው፤ ሁሉ ለማነጽ ይሁን።
27Ja kāds runā valodās, divi vai, lielākais, trīs un pēc kārtas, tad viens lai izskaidro;
27በልሳን የሚናገር ቢኖር ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው በተራቸው ይናገሩ አንዱም ይተርጉም፤
28Bet ja izskaidrotāja nav, tad lai viņš draudzē klusē un lai runā tikai sev un Dievam!
28የሚተረጉም ባይኖር ግን በማኅበር መካከል ዝም ይበልና ለራሱና ለእግዚአብሔር ይናገር።
29Arī pravieši lai runā divi vai trīs, bet citi lai apspriež!
29ነቢያትም ሁለት ወይም ሦስት ሆነው ይናገሩ ሌሎችም ይለዩአቸው፤
30Bet ja citam, kas tur sēž, rodas atklāsme, tad lai pirmais klusē!
30በዚያ ለሚቀመጥ ለሌላ ግን አንድ ነገር ቢገለጥለት ፊተኛው ዝም ይበል።
31Jo jūs visi pēc kārtas varat pravietot, lai visiem būtu pamācība un visiem - pamudinājums.
31ሁሉም እንዲማሩ ሁሉም እንዲመከሩ ሁላችሁ በእያንዳንዳችሁ ትንቢት ልትናገሩ ትችላላችሁ።
32Arī praviešu gari praviešiem pakļauti,
32የነቢያትም መናፍስት ለነቢያት ይገዛሉ፤
33Jo Dievs nav nevienprātības, bet miera Dievs, kā arī es visās svēto draudzēs mācu.
33እግዚአብሔርስ የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለምና፤ በቅዱሳንም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንዲህ ነው።
34Sievietes lai sanāksmēs klusē, jo viņām nav atļauts runāt, bet tām jābūt paklausīgām, kā arī likums to nosaka.
34ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፤ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።
35Bet ja tās grib ko uzzināt, tad lai mājās jautā saviem vīriem, jo sievietei nepieklājas runāt sanāksmē.
35ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር ነውና፥ ምንም ሊማሩ ቢወዱ በቤታቸው ባሎቻቸውን ይጠይቁ።
36Vai tad Dieva vārds no jums cēlies, vai tas pie jums vieniem nācis?
36ምን ነው? የእግዚአብሔር ቃል የወጣ ከእናንተ ነውን? ወይስ ወደ እናንተ ብቻ ደርሶአልን?
37Ja kādam šķiet, ka viņš ir pravietis vai gara cilvēks, tad viņam jāzina, ka tas, ko jums rakstu, ir Kunga pavēle.
37ማንም ነቢይ ወይም መንፈሳዊ የሆነ ቢመስለው ይህች የጻፍሁላችሁ የጌታ ትእዛዝ እንደ ሆነች ይወቅ፤
38Bet ja kads to neatzīst, tad arī viņš netiks atzīts.
38ማንም የማያውቅ ቢኖር ግን አይወቅ።
39Tātad, brāļi, centieties pravietot un neliedziet runāt valodās!
39ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ትንቢት ለመናገር በብርቱ ፈልጉ፥ በልሳኖች ከመናገርም አትከልክሉ፤
40Bet visam jānotiek pieklājīgi un kārtīgi.
40ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።