1Brāļi, es atgādinu jums evaņģēliju, ko es jums pasludināju, ko jūs pieņēmāt un kurā jūs arī stāvat,
1ወንድሞች ሆይ፥ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለሁ፤
2Caur ko jūs arī esat pestīti, ja jūs to paturat tādā veidā, kā es jums to pasludināju; citādi jūsu ticība ir veltīga.
2በከንቱ ካላመናችሁ በቀር፥ ብታስቡት፥ በምን ቃል እንደ ሰበክሁላችሁ አሳስባችኋለሁ።
3Jo vispirms es jums mācīju to, ko arī pats saņēmu, ka saskaņā ar Rakstiem Kristus ir miris par mūsu grēkiem,
3እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ። መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥
4Un ka Viņš ticis apbedīts, un ka Viņš saskaņā ar Rakstiem trešajā dienā augšāmcēlies,
4መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥
5Un ka Viņš parādījies Kēfam un pēc tam tiem vienpadsmit.
5ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤
6Vēlāk Viņš parādījās vairāk kā pieci simti brāļiem kopā esot, no kuriem daudzi vēl dzīvo līdz šim, bet daži jau aizmiguši.
6ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤
7Pēc tam Viņš parādījies Jēkabam, tad visiem apustuļiem;
7ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤
8Bet pēdīgi pēc visiem Viņš parādījās arī man, it kā kādam nelaikā dzimušajam.
8ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ።
9Jo es esmu mazākais starp apustuļiem un es neesmu cienīgs, ka mani sauc par apustuli, tādēļ ka es vajāju Dieva Baznīcu.
9እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ፤
10Bet, pateicoties Dieva žēlastībai, es esmu tas, kas es esmu, un Viņa žēlastība manī nebija nesekmīga, un es strādāju vairāk par viņiem visiem, tomēr ne es, bet Dieva žēlastība kopā ar mani.
10ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።
11Vai tas es, vai viņi, tā mēs sludinām, un tā jūs kļuvāt ticīgi.
11እንግዲህስ እኔ ብሆን እነርሱም ቢሆኑ እንዲሁ እንሰብካለን እንዲሁም አመናችሁ።
12Ja tad par Kristu sludina, ka Viņš no miroņiem augšāmcēlies, kā tad daži no jums saka, ka augšāmcēlšanās no miroņiem neesot?
12ክርስቶስ ከሙታን እንደ ተነሣ የሚሰበክ ከሆነ ግን ከእናንተ አንዳንዶቹ። ትንሣኤ ሙታን የለም እንዴት ይላሉ?
13Bet ja augšāmcelšanās no miroņiem nav, tad arī Kristus nav augšāmcēlies.
13ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሣማ፤
14Un ja Kristus nav augšāmcēlies, tad veltīga ir mūsu sludināšana, veltīga ir arī jūsu ticība.
14ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት፤
15Ja nav mirušo augšāmcelšanās, tad mēs esam arī Dieva viltus liecinieki, jo mēs būtu liecinājuši pret Dievu, ka Viņš Kristu uzmodinājis, bet Viņš to nebūtu uzmodinājis.
15ደግሞም። ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን በእግዚአብሔር ላይ ስለ መሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም።
16Jo ja mirušie augšām neceļas, tad arī Kristus nav augšāmcēlies.
16ሙታን የማይነሡ ከሆነ ክርስቶስ አልተነሣማ፤
17Un ja Kristus nav augšāmcēlies, tad veltīga ir jūsu ticība, jo jūs vēl esat savos grēkos.
17ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ።
18Tad arī tie, kas aizmiguši Kristū, ir pazuduši.
18እንግዲያስ በክርስቶስ ያንቀላፉት ደግሞ ጠፍተዋላ።
19Ja mēs uz Kristu ceram tikai šinī dzīvē, tad mēs esam tie nožēlojamākie starp visiem cilvēkiem.
19በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።
20Bet tagad Kristus ir no miroņiem augšāmcēlies kā pirmais starp mirušajiem,
20አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።
21Jo kā caur cilvēku nāve, tā arī caur cilvēku mirušo augšāmcēlšanās.
21ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።
22Un kā Ādamā visi mirst, tā arī Kristū tiks visi atdzīvināti,
22ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።
23Bet katrs pēc savas kārtas: Kristus kā pirmais, pēc tam tie, kas Kristum pieder, kas ticējuši uz Viņa atnākšanu.
23ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ተራ ይሆናል፤ ክርስቶስ እንደ በኩራት ነው፥ በኋላም በመምጣቱ ለክርስቶስ የሆኑት ናቸው፤
24Kad Viņš būs nodevis valstību Dievam un Tēvam, kad būs iznīcinājis katru valdību un varu, un spēku, pēc tam būs gals.
24በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል።
25Bet Viņam jāvalda, kamēr Viņš noliks visus ienaidniekus zem Viņa kājām.
25ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሩ በታች እስኪያደርግ ድረስ ሊነግሥ ይገባዋልና።
26Un kā pēdējais ienaidnieks tiks iznīcināta nāve, jo Viņš visu ir pakļāvis zem Tā kājām. Bet ja Viņš saka,
26የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው፤
27Ka viss Viņam pakļauts, tad, bez šaubām, izņemot To, kas Viņam visu pakļāvis.
27ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን። ሁሉ ተገዝቶአል ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው።
28Bet kad Viņam viss būs pakļauts, tad arī Dēls pats pakļausies Viņam, kas Tam visu pakļāva, lai visā viss būtu Dievs.
28ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል።
29Bez tam, ko darīs tie, kas liekas kristīties par mirušajiem? Ja vispār mirušie augšām necelsies, kāpēc tad kristīties par viņiem?
29እንዲያማ ካልሆነ፥ ስለ ሙታን የሚጠመቁ ምን ያደርጋሉ? ሙታንስ ከቶ የማይነሡ ከሆነ፥ ስለ እነርሱ የሚጠመቁ ስለ ምንድር ነው?
30Kāpēc arī mēs ik brīdi pastāvam briesmās?
30እኛስ ዘወትር በሚያስፈራ ኑሮ የምንኖር ስለ ምንድር ነው?
31Es mirstu ik dienas, tik tiešām, brāļi, kā jūs esat mans gods Kristū Jēzū, mūsu Kungā!
31በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ባለኝ በእናንተ ትምክህት እየማልሁ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕለት ዕለት እሞታለሁ።
32Ja es (kā cilvēks) Efezā cīnījos ar plēsīgajiem zvēriem, kāds man no tā labums, ja mirušie neceļas augšām? Ēdīsim un dzersim, jo rīt mēs mirsim!
32እንደ ሰው በኤፌሶን ከአውሬ ጋር ከታገልሁ፥ ሙታንስ የማይነሡ ከሆነ፥ ምን ይጠቅመኛል? ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ።
33Nepievilieties! Ļaunas valodas bojā labus tikumus.
33አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።
34Esiet modri jūs, taisnīgie, un negrēkojiet, ja daži Dievu nepazīst; to es saku jums par kaunu.
34በጽድቅ ንቁ ኃጢአትንም አትሥሩ፤ እግዚአብሔርን የማያውቁ አሉና፤ አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ።
35Bet ja kāds sacītu: Kā mirušie uzcelsies, kādā miesā tie atnāks?
35ነገር ግን ሰው። ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።
36Tu neprātīgais! Ko tu sēji, tas netop dzīvs, ja pirmāk nenomirst.
36አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም፤
37Un ko tu sēji, tā nav miesa, kas vēl taps, bet tu sēji kailu graudu, vai tas būtu kviešu, vai no kā cita.
37የምትዘራውም፥ ስንዴ ቢሆን ከሌላም ዓይነት የአንዱ ቢሆን፥ ቅንጣት ብቻ ነው እንጂ የምትዘራው የሚሆነውን አካል አይደለም፤
38Bet Dievs tam dod miesu, kā vēlēdamies, un ikkatrai sēklai dod savu īpatu miesu.
38እግዚአብሔር ግን እንደ ወደደ አካልን ይሰጠዋል ከዘሮችም ለእያንዳንዱ የገዛ አካሉን ይሰጠዋል።
39Ne ikkatra miesa ir tā pati miesa, jo citāda tā ir cilvēkiem, citāda dzīvniekiem, citāda putniem un citāda zivīm.
39ሥጋ ሁሉ አንድ አይደለም፥ የሰው ሥጋ ግን አንድ ነው፥ የእንስሳም ሥጋ ሌላ ነው፥ የወፎችም ሥጋ ሌላ ነው፥ የዓሣም ሥጋ ሌላ ነው።
40Ir arī debesu ķermeņi un zemes ķermeņi; bet citāds ir debesu un citāds zemes ķermeņu krāšņums.
40ደግሞ ሰማያዊ አካል አለ፥ ምድራዊም አካል አለ፤ ነገር ግን የሰማያዊ አካል ክብር ልዩ ነው፥ የምድራዊም አካል ክብር ልዩ ነው።
41Citāds spožums ir saulei, citāds spožums mēnesim un citāds spožums zvaigznēm; pat zvaigzne no zvaigznes atšķiras spožumā.
41የፀሐይ ክብር አንድ ነው የጨረቃም ክብር ሌላ ነው የከዋክብትም ክብር ሌላ ነው፤ በክብር አንዱ ኮከብ ከሌላው ኮከብ ይለያልና።
42Tā arī augšāmcelšanās no miroņiem. Sēts tiek iznīcībā, augšāmcelsies neiznīcībā.
42የሙታን ትንሣኤ ደግሞ እንዲሁ ነው። በመበስበስ ይዘራል፥ ባለመበስበስ ይነሣል፤
43Sēts tiek negodā, augšāmcelsies godībā; sēts top nespēkā, augšāmcelsies spēkā.
43በውርደት ይዘራል፥ በክብር ይነሣል፤ በድካም ይዘራል፥ በኃይል ይነሣል፤
44Sēta top dabīga miesa, augšāmcelsies garīga miesa. Ja ir dabīga miesa, tad ir arī garīga, kā tas rakstīts:
44ፍጥረታዊ አካል ይዘራል፥ መንፈሳዊ አካል ይነሣል። ፍጥረታዊ አካል ካለ መንፈሳዊ አካል ደግሞ አለ።
45Pirmais cilvēks Ādams kļuva dzīva dvēsele, pēdējais Ādams - atdzīvinātājs Gars.
45እንዲሁ ደግሞ። ፊተኛው ሰው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ ተብሎ ተጽፎአል፤ ኋለኛው አዳም ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ።
46Bet pirms nekā garīgais, ir dabīgais, pēc tam garīgais.
46ነገር ግን አስቀድሞ ፍጥረታዊው ቀጥሎም መንፈሳዊው ነው እንጂ መንፈሳዊው መጀመሪያ አይደለም።
47Pirmais cilvēks no zemes - laicīgs; otrs Cilvēks no debesīm - debesu.
47የፊተኛው ሰው ከመሬት መሬታዊ ነው፤ ሁለተኛው ሰው ከሰማይ ነው።
48Kāds tas, kas no zemes, tādi arī laicīgie, un kāds Tas, kas no debesīm, tādi arī tie, kas no debesīm.
48መሬታዊው እንደ ሆነ መሬታውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው፥ ሰማያዊው እንደ ሆነ ሰማያውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው።
49Tātad, kā mēs bijām tā attēls, kas no zemes, tā lai esam arī Tā attēls, kas no debesīm.
49የዚያንም የመሬታዊውን መልክ እንደ ለበስን የሰማያዊውን መልክ ደግሞ እንለብሳለን።
50Brāļi, bet to es saku: miesa un asinis nevar iemantot Dieva valstību, nedz iznīcība iemantos neiznīcību.
50ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ። ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም።
51Lūk, es jums saku noslēpumu: Mēs visi celsimies augšām, bet ne visi tiksim pārveidoti,
51እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበት ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።
52Piepeši, acumirklī, pēdējai bazūnei atskanot; jo bazūne atskanēs, un mirušie celsies augšām neiznīcībā, un mēs tapsim pārveidoti.
53ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና።
53Jo šim iznīcīgajam jātērpjas neiznīcībā, un šeit mirstīgajam jātērpjas nemirstībā.
54ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ። ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።
54Bet kad šeit mirstīgais būs tērpies nemirstībā, tad piepildīsies vārdi, kas rakstīti: Nāve ir aprīta uzvarā.
55ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ?
55Nāve, kur ir tava uzvara? Nāve, kur ir tavs dzelonis?
56የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤
56Bet nāves dzelonis ir grēks, un grēka spēks ir likums.
57ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።
57Bet pateicība Dievam, kas mums devis uzvaru caur mūsu Kungu Jēzu Kristu!
58ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።
58Tāpēc, mani mīļie brāļi, esiet pastāvīgi un nesatricināmi, vienmēr centīgi Kunga darbā, zinādami, ka jūsu darbs nav veltīgs Kungā!