1Bet ziedojumu vākšanu, kas notiek svēto labā, izdariet tāpat, kā es to noteicu Galatijas draudzēm.
1ለቅዱሳንም ገንዘብን ስለ ማዋጣት፥ ለገላትያ አብያተ ክርስቲያናት እንደ ደነገግሁት እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
2Lai ikviens no jums pirmajā nedēļas dienā atliek un uzglabā, kas kuram labpatiks, lai nevajadzētu vākt ziedojumus tad, kad es atnākšu.
2እኔ ስመጣ ይህ የገንዘብ ማዋጣት ያን ጊዜ እንዳይሆን፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በየሳምንቱ በፊተኛው ቀን እንደ ቀናው መጠን እያስቀረ በቤቱ ያስቀምጥ።
3Bet kad es būšu pie jums, tad es sūtīšu tos, kurus jūs rakstiski atzīsiet par piemērotiem, uz Jeruzalemi, lai aiznes jūsu dāvanas.
3ስመጣም ማናቸውም ቢሆኑ የታመኑ የሚመስሉአችሁ ሰዎች ቸርነታችሁን ወደ ኢየሩሳሌም ያደርሱ ዘንድ ደብዳቤ ሰጥቼ እልካቸዋለሁ፤
4Bet ja izrādīsies, ka ir vēlams, lai arī es ietu, tad viņi ies reizē ar mani.
4እኔ ደግሞ ልሄድ የሚገባኝ ብሆን ከእኔ ጋር አብረው ይሄዳሉ።
5Tomēr es nākšu pie jums tad, kad būšu pārstaigājis Maķedoniju, jo caur Maķedoniju es iešu.
5በመቄዶንያም ሳልፍ ወደ እናንተ እመጣለሁ፤ በመቄዶንያ አድርጌ አልፋለሁና፤
6Bet pie jums es varbūt uzkavēšos, vai pat pārziemošu, lai jūs mani aizvadītu turp, kur iešu.
6እናንተም ወደምሄድበት ወደ ማናቸውም ስፍራ በጉዞዬ እንድትረዱኝ ምናልባት በእናንተ ዘንድ እቆይ ወይም እከርም ይሆናል።
7Jo es negribu tikai garām ejot jūs redzēt, bet ceru, ja Kungs atļaus, kādu laiku palikt pie jums.
7አሁን እግረ መንገዴን ሳልፍ ልጎበኛችሁ አልወድምና፤ ጌታ ቢፈቅደው የሆነውን ዘመን በእናንተ ዘንድ ልሰነብት ተስፋ አደርጋለሁና።
8Efezā es palikšu līdz Vasarsvētkiem;
8በኤፌሶን ግን እስከ በዓለ ኀምሳ ድረስ እሰነብታለሁ።
9Jo durvis man atvērušās lielas un plašas, bet arī pretinieku daudz.
9ሥራ የሞላበት ትልቅ በር ተከፍቶልኛልና ተቃዋሚዎችም ብዙ ናቸው።
10Bet kad atnāks Timotejs, lūkojiet, ka viņš justos pie jums drošībā, jo viņš strādā Kunga darbu tāpat kā es.
10ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።
11Neviens lai viņu nenievā, bet pavadiet viņu mierā, lai viņš nāk pie manis, jo es gaidu viņu kopā ar brāļiem.
11ነገር ግን ከወንድሞቹ ጋር እጠብቀዋለሁና ወደ እኔ ይመጣ ዘንድ በሰላም በጉዞው እርዱት።
12Un par brāli Apollu es jums ziņoju, ka es viņu ļoti lūdzu, lai viņš kopā ar brāļiem aiziet pie jums, bet viņam nebija prātā tagad iet, bet viņš aizies, tiklīdz viņam būs laiks.
12ስለ ወንድማችን ስለ አጵሎስ ግን ከወንድሞቹ ጋር ወደ እናንተ ሊሄድ እጅግ አድርጌ ለምኜው ነበር፤ ዛሬም ለመምጣት ከቶ ፈቃድ አልነበረውም፥ ሲመቸው ግን ይመጣል።
13Esiet modri, pastāviet ticībā, darbojieties vīrišķīgi un esiet stipri!
13ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።
14Visi jūsu darbi lai notiek mīlestībā!
14በእናንተ ዘንድ ሁሉ በፍቅር ይሁን።
15Bet es jūs, brāļi, lūdzu: jūs pazīstat Stefanas namu; viņi ir Ahajas pirmkristītie un nodevušies kalpošanai svētajiem.
15ወንድሞች ሆይ፥ የእስጢፋኖስ ቤተ ሰዎች የአካይያ በኩራት እንደ ሆኑ ቅዱሳንንም ለማገልገል ራሳቸውን እንደ ሰጡ ታውቃላችሁ፤
16Esiet arī jūs padevīgi viņiem un katram, kas darbojas līdz un strādā.
16እንደ እነርሱ ላሉትና አብሮ ለሚሠራ ለሚደክምም ሁሉ እናንተም እንድትገዙ እለምናችኋለሁ።
17Bet es priecājos par Stefanas un Fortunāta, un Ahaika klātbūtni, jo viņi aizvieto to, kas trūka no jūsu puses,
17በእስጢፋኖስና በፈርዶናጥስ በአካይቆስም መምጣት ደስ ይለኛል፥ እናንተ ስለሌላችሁ የጎደለኝን ፈጽመዋልና፤ መንፈሴንና መንፈሳችሁን አሳርፈዋልና።
18Jo viņi atspirdzināja manu un jūsu garu. Tāpēc atzīstiet viņus par tādiem;
18እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን እወቁአቸው።
19Āzijas draudzes jūs sveicina. Akvila un Priskilla kopā ar savas mājas draudzi jūs daudzreiz sveicina Kungā. Pie viņiem es arī mājoju.
19የእስያ አብያተ ክርስቲያናት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። አቂላና ጵርስቅላ በቤታቸው ካለች ቤተ ክርስቲያን ጋር በጌታ እጅግ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
20Visi brāļi jūs sveicina. Sveiciniet viens otru ar svētu skūpstu!
20ወንድሞች ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ።
21Sveiciens ar manu, Pāvila, roku.
21እኔ ጳውሎስ ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ ጽፌአለሁ።
22Ja kāds nemīl mūsu Kungu Jēzu Kristu, tas lai tiek pazudināts! Maran, ata.
22ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን። ጌታችን ሆይ፥ ና።
23Mūsu Kunga Jēzus Kristus žēlastība lai ir ar jums!
23የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።
24Mana mīlestība lai ir ar jums visiem Kristū Jēzū! Amen.
24ፍቅሬ በክርስቶስ ኢየሱስ ከሁላችሁ ጋር ነው። አሜን።