Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

1 Corinthians

4

1Tātad lai katrs cilvēks mūs atzīst par Kristus kalpiem un Dieva noslēpumu pārvaldniekiem.
1እንዲሁ ሰው እኛን እንደ ክርስቶስ ሎሌዎችና እንደ እግዚአብሔር ምሥጢር መጋቢዎች ይቍጠረን።
2No pārvaldniekiem jau prasa, lai katrs būtu uzticams.
2እንደዚህም ሲሆን፥ በመጋቢዎች ዘንድ የታመነ ሆኖ መገኘት ይፈለጋል።
3Bet tas man nav svarīgi, ka jūs vai kāda cilvēku tiesa mani tiesā, bet arī pats sevi es netiesāju.
3ነገር ግን በእናንተ ዘንድ ወይም በሌላ ሰው ዘንድ ብፈረድ ለእኔ ምንም አይደለም፤ እኔም በራሴ እንኳ አልፈርድም፤
4Jo es gan nekā neapzinos, bet tas mani vēl neattaisno. Kungs ir mans tiesnesis.
4በራሴ ላይ ምንም አላውቅምና፥ ነገር ግን በዚህ አልጸድቅም፤ እኔን የሚፈርድ ግን ጌታ ነው።
5Tāpēc netiesājiet pirms laika, kamēr atnāks Kungs. Viņš apgaismos tumsību noslēpumus un atklās siržu nodomus, un tad katram būs gods no Dieva.
5ስለዚህም በጨለማ የተሰወረውን ደግሞ ወደ ብርሃን የሚያወጣ የልብንም ምክር የሚገልጥ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ጊዜው ሳይደርስ አንዳች አትፍረዱ፤ በዚያን ጊዜም ለእያንዳንዱ ምስጋናው ከእግዚአብሔር ዘንድ ይሆናል።
6Bet, brāļi, to es attiecināju uz sevi un Apollu jūsu labad, lai jūs no mums mācītos ne vairāk par to, kas rakstīts, vienam pret otru nekļūt uzpūtīgam cita dēļ.
6ወንድሞች ሆይ፥ ስለ አንዱ በአንዱ ላይ አንዳችሁም እንዳይታበዩ። ከተጻፈው አትለፍ የሚለውን በእኛ ትማሩ ዘንድ፥ ይህን በእናንተ ምክንያት ስለ ራሴና ስለ አጵሎስ እንደ ምሳሌ ተናገርሁ።
7Jo kas tev devis priekšrocības? Bet kas tev ir, ko tu nebūtu saņēmis? Un ja tu esi saņēmis, kāpēc lielies, it kā tu nebūtu saņēmis?
7አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጎሃል? ያልተቀበልኸውስ ምን አለህ? የተቀበልህ ከሆንህ ግን እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለ ምንድር ነው?
8Jūs jau esat paēduši, jau bagāti kļuvuši; jūs valdāt bez mums; un kaut jūs valdītu, lai arī mēs reizē ar jums valdītu!
8አሁን ጠግባችኋል፤ አሁንስ ባለ ጠጎች ሆናችኋል፤ ያለ እኛ ነግሣችኋል፤ እኛ ደግሞ ከእናንተ ጋር እንድንነግሥ ብትነግሡ መልካም ይሆን ነበር።
9Jo man šķiet, ka Dievs mums, apustuļiem, it kā nāvei lemtiem ierādījis pēdējo vietu, jo mēs esam kļuvuši par izbrīnu pasaulei un eņģeļiem, un cilvēkiem.
9ለዓለም ለመላእክትም ለሰዎችም መጫወቻ ሆነናልና፤ እግዚአብሔር እኛን ሐዋርያቱን ሞት እንደ ተፈረደባቸው ሰዎች ከሁሉ ይልቅ የኋለኞች እንዳደረገን ይመስለኛልና።
10Mēs neprātīgi Kristus dēļ, bet jūs gudri Kristū; mēs nespēcīgi, bet jūs stipri; jūs cienīti, bet mēs nicināti.
10እኛ ስለ ክርስቶስ ሞኞች ነን እናንተ ግን በክርስቶስ ልባሞች ናችሁ፤ እኛ ደካሞች ነን እናንተ ግን ኃይለኞች ናችሁ፤ እናንተ የከበራችሁ ናችሁ እኛ ግን የተዋረድን ነን።
11Līdz pat šai stundai ciešam arī izsalkumu un slāpes, esam arī kaili un tiekam dūrēm sisti, kā arī esam bez pajumtes;
11እስከዚህ ሰዓት ድረስ እንራባለን፥ እንጠማለን፥ እንራቆታለን፥ እንጐሰማለን፥ እንንከራተታለን፥
12Un mēs pūlamies, strādādami savām rokām. Mūs lād, bet mēs svētām; mūs vajā, bet mēs paciešam;
12በገዛ እጃችን እየሠራን እንደክማለን፤ ሲሰድቡን እንመርቃለን፥ ሲያሳድዱን እንታገሣለን፥ ክፉ ሲናገሩን እንማልዳለን፤
13Mūs zaimo, bet mēs aizlūdzam; mēs esam kļuvuši it kā šīs pasaules atkritumi, kā no visiem atmetami līdz pat šim laikam.
13እስከ አሁን ድረስ የዓለም ጥራጊ የሁሉም ጉድፍ ሆነናል።
14To es rakstu nevis jūsu apkaunošanai, bet pamācīdams kā savus vismīļākos bērnus.
14እንደምወዳችሁ ልጆቼ አድርጌ ልገሥጻችሁ እንጂ ላሳፍራችሁ ይህን አልጽፍም።
15Ja jums arī Kristū būtu desmit tūkstoši skolotāju, tad tomēr nedaudz tēvu, jo es caur evaņģēliju esmu jūs dzemdinājis Kristū Jēzū.
15በክርስቶስ አእላፍ ሞግዚቶች ቢኖሩአችሁ ብዙ አባቶች የሉአችሁም እኔ በክርስቶስ ኢየሱስ በወንጌል ወልጄአችኋለሁና።
16Tātad es jūs lūdzu: sekojiet man, kā arī es Kristum!
16እንግዲህ እኔን የምትመስሉ ሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ።
17Tāpēc es sūtīju pie jums Timoteju, kas ir mans vismīļais un uzticīgais dēls Kungā; viņš jums atgādinās manu mācību Kristū Jēzū, kā es visur un katrā draudzē mācu.
17ስለዚህ የምወደውንና የታመነውን በጌታ ልጄ የሆነውን ጢሞቴዎስን ልኬላችኋለሁ፥ እኔም በየስፍራው በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንደማስተምር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚሆነውን መንገዴን እርሱ ያሳስባችኋል።
18Daži ir uzpūtušies, it kā es vairs nenākšot pie jums.
18አንዳንዱ ግን ወደ እናንተ የማልመጣ እየመሰላቸው የታበዩ አሉ፤
19Ja Dievs gribēs, es drīz nākšu pie jums; un es iepazīšos ne ar uzpūtīgo vārdiem, bet ar viņa spēku.
19ነገር ግን ጌታ ቢፈቅድ ፈጥኜ ወደ እናንተ እመጣለሁ፥ የትዕቢተኞችንም ኃይል አውቃለሁ እንጂ ቃላቸውን አይደለም፤
20Jo Dieva valstība pastāv ne vārdos, bet spēkā.
20የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ነው እንጂ በቃል አይደለምና።
21Ko jūs gribat? Vai lai es nāku pie jums ar rīksti, vai mīlestībā un lēnprātības garā?
21ምን ትወዳላችሁ? በበትር ወይስ በፍቅርና በየውሃት መንፈስ ልምጣባችሁን?