Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

1 Corinthians

3

1Brāļi, arī es nevarēju ar jums runāt kā ar garīgiem, bet kā ar miesīgiem, kā ar bērniem Kristū.
1እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ የሥጋ እንደ መሆናችሁ፥ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም።
2Es jums devu pienu dzeršanai, ne cietu barību, jo jūs vēl nevarējāt, bet arī tagad vēl nevarat, jo jūs vēl esat miesīgi,
2ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ፤
3Kamēr starp jums pastāv skaudība un ķildas, vai jūs neesat miesīgi un nedzīvojat kā miesīgi cilvēki?
3ገና ሥጋውያን ናችሁና እስከ አሁን ድረስ ገና አትችሉም። ቅናትና ክርክር ስለሚገኝባችሁ ሥጋውያን መሆናችሁ አይደላችሁምን? እንደ ሰው ልማድስ አትመላለሱምን?
4Jo ja kāds saka: Es esmu Pāvila, bet cits: Es esmu Apolla, vai tad jūs neesat cilvēki? Jo kas ir Apolls vai kas ir Pāvils?
4አንዱ። እኔ የጳውሎስ ነኝ፥ ሁለተኛውም። እኔ የአጵሎስ ነኝ ቢል ሰዎች ብቻ መሆናችሁ አይደለምን?
5Tie ir Tā kalpi, uz kuru jūs esat ticējuši tā, kā Kungs katram to devis.
5አጵሎስ እንግዲህ ምንድር ነው? ጳውሎስስ ምንድር ነው? በእነርሱ እጅ ያመናችሁ አገልጋዮች ናቸው፤ ለእያንዳንዳቸውም ጌታ እንደ ሰጣቸው ያገለግላሉ።
6Es dēstīju, Apolls laistīja, bet Dievs deva augumu.
6እኔ ተከልሁ አጵሎስም አጠጣ ነገር ግን እግዚአብሔር ያሳድግ ነበር፤
7Tāpēc ne tas ir kas, kas dēsta, un ne tas, kas laista, bet Dievs, kas audzē.
7እንግዲያስ የሚያሳድግ እግዚአብሔር እንጂ የሚተክል ቢሆን ወይም የሚያጠጣ ቢሆን አንዳች አይደለም።
8Bet dēstītājs un laistītājs ir līdzīgi. Katrs saņems savu algu saskaņā ar savu darbu;
8የሚተክልና የሚያጠጣ አንድ ናቸው፥ ነገር ግን እያንዳንዱ እንደ ራሱ ድካም መጠን የራሱን ደመወዝ ይቀበላል።
9Jo mēs esam Dieva palīgi, jūs esat Dieva tīrums, Dieva celtne.
9የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንፃ ናችሁ፤ ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና።
10Saskaņā ar Dieva žēlastību, kas man dota, es kā gudrs namdaris ieliku pamatu, bet cits uz tā ceļ. Bet lai katrs pielūko, kā viņš uz tā ceļ.
10የእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ተሰጠኝ መጠን እንደ ብልሃተኛ የአናጺ አለቃ መሠረትን መሠረትሁ፥ ሌላውም በላዩ ያንጻል። እያንዳንዱ ግን በእርሱ ላይ እንዴት እንዲያንጽ ይጠንቀቅ።
11Jo citu pamatu neviens nevar likt, kā to, kas jau likts, tas ir Jēzus Kristus.
11ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
12Vai kāds uz šī pamata ceļ zeltu, sudrabu, dārgakmeņus, koku, sienu, salmus,
12ማንም ግን በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ቢሆን በብርም በከበረ ድንጋይም በእንጨትም በሣርም ወይም በአገዳ ቢያንጽ፥ የእያንዳንዱ ሥራ ይገለጣል፤
13To parādīs katra darbs. Kunga diena to atklās, jo tā parādīsies ar uguni, un kāds kura darbs ir, to pārbaudīs uguns.
13በእሳት ስለሚገለጥ ያ ቀን ያሳያልና፥ የእያንዳንዱም ሥራ እንዴት መሆኑን እሳቱ ይፈትነዋል።
14Ja kāda darbs, ko tas cēlis, pastāvēs, tas saņems algu.
14ማንም በእርሱ ላይ ያነጸው ሥራ ቢጸናለት ደመወዙን ይቀበላል፤
15Ja kāda darbs sadegs, tas cietīs zaudējumu, bet pats tiks pestīts, bet gan kā caur uguni.
15የማንም ሥራ የተቃጠለበት ቢሆን ይጎዳበታል፥ እርሱ ራሱ ግን ይድናል ነገር ግን በእሳት እንደሚድን ይሆናል።
16Vai nezināt, ka jūs esat Dieva svētnīca un ka Dieva Gars mājo jūsos?
16የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?
17Ja kāds Dieva svētnīcu apgāna, to Dievs iznīcinās. Jo Dieva svētnīca ir svēta, un tā esat jūs.
17ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።
18Lai neviens sevi nepieviļ! Ja kāds uzskata sevi gudru šinī pasaulē, tam jātop neprātīgam, lai kļūtu saprātīgs.
18ማንም ራሱን አያታልል፤ ከእናንተ ማንም በዚች ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ሞኝ ይሁን።
19Jo šīs pasaules gudrība ir Dievam neprātība. Jo ir rakstīts: Es notveršu gudros viņu viltībā.
19የዚህች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤ ደግሞም። ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።
20Un atkal: Kungs zina gudro domas, ka tās ir tukšas.
21ስለዚህም ማንም በሰው አይመካ። ነገር ሁሉ የእናንተ ነውና፤
21Tāpēc neviens lai nelielās ar cilvēkiem!
22ጳውሎስ ቢሆን አጵሎስም ቢሆን ኬፋም ቢሆን ዓለምም ቢሆን ሕይወትም ቢሆን ሞትም ቢሆን ያለውም ቢሆን የሚመጣውም ቢሆን፥
22Jo viss ir jūsu: vai tas būtu Pāvils, vai Apolls, vai Kēfa, vai pasaule, vai dzīvība, vai nāve, vai tagadne, vai nākotne, viss pieder jums;
23ሁሉ የእናንተ ነው፥ እናንተም የክርስቶስ ናችሁ ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው።
23Bet jūs piederat Kristum un Kristus - Dievam.