Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

1 Timothy

3

1Tas ir patiess vārds: ja kas alkst bīskapa amata, tas tiecas pēc laba darba.
1ማንም ኤጲስ ቆጶስነትን ቢፈልግ መልካምን ሥራ ይመኛል የሚለው ቃል የታመነ ነው።
2Tātad bīskapam jābūt nevainojamam, vienas sievas vīram, sātīgam, prātīgam, cienīgam, godājamam, viesmīlīgam, mācītam,
2እንግዲህ ኤጲስ ቆጶስ እንዲህ ሊሆን ይገባዋል፤ የማይነቀፍ፥ የአንዲት ሚስት ባል፥ ልከኛ፥ ራሱን የሚገዛ፥ እንደሚገባው የሚሰራ፥ እንግዳ ተቀባይ፥ ለማስተማር የሚበቃ፥
3Ne dzērājam, ne kauslim, bet lēnprātīgam, ne ķildīgam, ne mantkārīgam,
3የማይሰክር፥ የማይጨቃጨቅ ነገር ግን ገር የሆነ፥ የማይከራከር፥ ገንዘብን የማይወድ፥
4Bet labam sava nama pārvaldniekam, kam bērni paklausa pilnīgā tikumībā.
4ልጆቹን በጭምትነት ሁሉ እየገዛ የራሱን ቤት በመልካም የሚያስተዳድር፤
5Bet ja kas nemāk valdīt pār savu namu, kā tas gādās par Dieva Baznīcu?
5ሰው ግን የራሱን ቤት እንዲያስተዳድር ባያውቅ፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዴት ይጠብቃታል?
6Ne jaunam ticībā, lai nekļūtu lepns un neiekristu velna tiesa.
6በትዕቢት ተነፍቶ በዲያቢሎስ ፍርድ እንዳይወድቅ፥ አዲስ ክርስቲያን አይሁን።
7Viņam jābūt labā slavā pie tiem, kas ir ārpusē, lai neiekristu neslavā un ļaunā gara slazdos.
7በዲያቢሎስ ነቀፋና ወጥመድም እንዳይወድቅ፥ በውጭ ካሉት ሰዎች ደግሞ መልካም ምስክር ሊኖረው ይገባዋል።
8Tāpat diakoniem jābūt godājamiem, ne divkosīgiem, ne pārmērīgiem vīna lietotājiem, ne negodīgas peļņas kāriem,
8እንዲሁም ዲያቆናት ጭምቶች፥ በሁለት ቃል የማይናገሩ፥ ለብዙ ወይን ጠጅ የማይጎመጁ፥
9Tādiem, kas ticības noslēpumu glabā tīrā sirdsapziņā.
9ነውረኛ ረብ የማይወዱ፥ በንጹሕ ሕሊና የሃይማኖትን ምሥጢር የሚይዙ ሊሆኑ ይገባቸዋል።
10Bet tie iepriekš jāpārbauda un, ja viņiem pārkāpumu nav, tad lai kalpo.
10እነዚህም ደግሞ አስቀድሞ ይፈተኑ፥ ከዚያም በኋላ ያለ ነቀፋ ቢሆኑ በዲቁና ሥራ ያገልግሉ።
11Tāpat sievietēm jābūt cienījamām, ne mēlnesīgām, sātīgām, visā uzticīgām.
11እንዲሁም ሴቶች ጭምቶች፥ የማያሙ፥ ልከኞች፥ በነገር ሁሉ የታመኑ ሊሆኑ ይገባቸዋል።
12Diakoniem jābūt vienas sievas vīriem, kas labi valda savus bērnus un savu namu;
12ዲያቆናት ልጆቻቸውንና የራሳቸውን ቤቶች በመልካም እየገዙ እያንዳንዳቸው የአንዲት ሴት ባሎች ይሁኑ።
13Jo tie, kas labi pilda savu pienākumu, iegūst goda vietu un stipru cerību ticībā, kas ir Kristū Jēzū.
13በዲቁና ሥራ በመልካም ያገለገሉ ለራሳቸው ትልቅ ማዕርግና በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው እምነት ብዙ ድፍረት ያገኛሉ።
14šo es tev rakstu, cerēdams drīzumā nākt pie tevis;
14ፈጥኜ ወደ አንተ እንድመጣ ተስፋ አድርጌ ይህን እጽፍልሃለሁ።
15Bet ja es aizkavējos, lai tu zinātu, kā jāizturas Dieva namā, kas ir dzīvā Dieva Baznīca, patiesības balsts un pamats.
15ብዘገይ ግን፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።
16Un patiesi liels ir dievbijības noslēpums. Tas ir parādījies miesīgi, apliecināts garā, eņģeļi to skatījuši, tautām tas sludināts, pasaulē ticēts, godībā uzņemts.
16እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ።