Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

2 Corinthians

10

1Bet es, Pāvils, kas jūsu klātbūtnē esot pazemīgs, bet prombūtnē drošsirdīgs pret jums, lūdzu jūs Kristus lēnprātības un laipnības dēļ.
1እኔም ራሴ ጳውሎስ፥ በእናንተ ዘንድ ፊት ለፊት ሳለሁ ትሑት የሆንሁ፥ ከእናንተ ግን ብርቅ የምደፍራችሁ፥ በክርስቶስ የዋህነትና ገርነት እመክራችኋለሁ፤
2Un es jūs lūdzu, lai man nevajadzētu, pie jums esot, uzstāties ar tādu drošsirdību, ar kādu esmu apņēmies uzstāties pret dažiem, kas domā, ka mēs dzīvojam miesai.
2በዓለማዊ ልማድ እንደምንመላለስ በሚቆጥሩን በአንዳንዶች ላይ አምኜ ልደፍር አስባለሁ፥ በዚያ እምነት ግን ከእናንተ ጋር ሆኜ እንዳልደፍር እለምንችኋለሁ።
3Jo mēs gan miesā dzīvojam, bet nekarojam miesīgi.
3በሰው ልማድ ምንም እንኳ የምንመላለስ ብንሆን፥ እንደ ሰው ልማድ አንዋጋም፤
4Mūsu cīņas ieroči nav miesīgi, bet ar Dievu tie ir spējīgi sagraut cietokšņus; mēs apgāžam lēmumus
4የጦር ዕቃችን ሥጋዊ አይደለምና፥ ምሽግን ለመስበር ግን በእግዚአብሔር ፊት ብርቱ ነው፤
5Un katru augstprātību, kas paceļas pret Dieva atzīšanu, un ņemam gūstā visus prātus, lai tie kalpotu Kristum.
5የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥
6Un esam gatavi nosodīt katru nepaklausību, tiklīdz jūsu paklausība būs pilnīga.
6መታዘዛችሁም በተፈጸመች ጊዜ አለመታዘዝን ሁሉ ልንበቀል ተዘጋጅተናል።
7Vērojiet to, kas acu priekšā! Ja kāds ir sevī pārliecināts, ka viņš pieder Kristum, tad lai tas pats sevi padomā: kā viņš pieder Kristum, tā arī mēs.
7በፊታችሁ ያለውን ተመልከቱ። ማንም የክርስቶስ መሆኑን ተረድቶ ቢሆን፥ ይህን እንደ ገና በራሱ ይቁጠረው፤ እርሱ የክርስቶስ እንደ ሆነ እኛ ደግሞ እንዲሁ ነን።
8Un ja es vēl vairāk lepotos ar varu, ko Kungs mums devis jūsu stiprināšanai, bet ne jūsu graušanai, arī tad es nepalikšu kaunā.
8ጌታ እናንተን ለማነጽ እንጂ እናንተን ለማፍረስ ያይደለ በሰጠው በሥልጣናችን ከፊት ይልቅ ብመካ እንኳ አላፍርም።
9Bet nedomājiet, ka es ar vēstulēm gribētu jūs iebaidīt!
9በመልእክቶቼ የማስደነግጣችሁ አይምሰላችሁ።
10Jo tie gan saka, ka viņa vēstules ir svarīgas un spēcīgas, bet viņa personīgā uzstāšanās ir vāja, un viņa runa nenozīmīga.
10መልእክቶቹስ ከባድና ኃይለኛ ናቸው፥ ሰውነቱ ግን ሲታይ ደካማ ነው፥ ንግግሩም የተናቀ ነው ይላሉና።
11Tādi lai iegaumē sekojošo: kādi mēs esam prombūtnē vārdos savās vēstulēs, tādi arī klātesot darbos.
11እንዲሁ የሚል ይህን ይቁጠረው፤ በሩቅ ሳለን በመልእክታችን በኩል በቃል እንዳለን፥ በፊቱ ደግሞ ሳለን በሥራ እንዲሁ ነን።
12Jo mēs neuzdrošināmies sevi pieskaitīt vai pielīdzināt tādiem, kas sevi ieteic; bet mēs mērojam sevi pēc tā, kas mēs sevī esam un salīdzinām sevi ar mums pašiem.
12ራሳቸውን ከሚያመሰግኑ ከአንዳንዶች ጋር ራሳችንን ልንቆጥር ወይም ራሳችንን ልናስተያይ አንደፍርምና፤ ነገር ግን እነርሱ ራሳቸውን ከራሳቸው ጋር ሲያመዛዝኑ፥ ራሳቸውንም ከራሳቸው ጋር ሲያስተያዩ፥ አያስተውሉም።
13Bet mēs neleposimies pārmērīgi, bet saskaņā ar mēra paraugu, ko Dievs mums spraudis. Pēc šī mēra mēs sniedzamies līdz jums.
13እኛ ግን እግዚአብሔር እንደ ወሰነልን እስከ እናንተ እንኳ እንደሚደርስ እንደ ክፍላችን ልክ እንጂ ያለ ልክ አንመካም።
14Mēs nepārspīlējam, it kā mēs nebūtu nonākuši līdz jums; mēs taču atnesām jums Kristus evaņģēliju.
14ወደ እናንተ እንደማንደርስ አድርገን ከመጠን አናልፍምና፥ የክርስቶስን ወንጌል በመስበክ እስከ እናንተ እንኳ ደርሰናልና፤
15Mēs bez mēra nelielīsimies ar svešiem darbiem, bet mēs ceram, ka, pieaugot jūsu ticībai, mēs savas darbības apjomā iegūsim jūsu atzinību pārpilnībā,
15በሌሎች ድካም ያለ ልክ አንመካም፥ ነገር ግን እምነታችሁ ሲያድግ ከእናንተ ወዲያ ባለው አገር እስክንሰብክ ሥራችንን እየጨመርን፥ በክፍላችን በእናንተ ዘንድ እንድንከብር ተስፋ እናደርጋለን፤ በሌላው ክፍል ስለ ተዘጋጀው ነገር አንመካም።
16Lai varētu sludināt evaņģēliju pāri jūsu robežām, nemaz nedižojoties ar to, kas jau padarīts svešā darba laukā.
17የሚመካ ግን በጌታ ይመካ፤ እግዚአብሔር የሚያመሰግነው እንጂ ራሱን የሚያመሰግን እርሱ ተፈትኖ የሚወጣ አይደለምና።
17Bet kas lielās, lai lielās Kungā!
18Jo ne tas ir cienīgs, kas sevi ieteic, bet ko Kungs ieteic.