Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

2 Corinthians

11

1Kaut jūs mazliet paciestu mani manā neprātībā! Bet jūs jau ciešat mani.
1በጥቂቱ ሞኝነቴ ብትታገሡኝ መልካም ይሆን ነበር፤ ቢሆንም በእርግጥ ታገሡኝ።
2Jo es cenšos par jums ar Dieva centību; es saderināju jūs vienam Vīram, lai kā nevainīgu jaunavu stādītu Kristum priekšā.
2በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤
3Bet es baidos, ka jūs neatkristu no Kristus vienkāršības un jūsu domas netiktu sagandētas, tāpat kā čūska pievīla Ievu ar savu viltību.
3ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ።
4Bet ja kāds nāk un sludina citu Kristu nekā to, ko esam sludinājuši, vai saņemat citu garu nekā to, ko esat saņēmuši, vai citu evaņģēliju, nekā to, ko pieņēmuši, tad jūs to labprāt ciešat.
4የሚመጣውም ያልሰበክነውን ሌላ ኢየሱስ ቢሰብክ፥ ወይም ያላገኛችሁትን ልዩ መንፈስ ወይም ያልተቀበላችሁትን ልዩ ወንጌል ብታገኙ፥ በመልካም ትታገሡታላችሁ።
5Man šķiet, ka es ne mazāk par tiem dižapustuļiem esmu darījis.
5ከእነዚህ ከዋነኞቹ ሐዋርያት በአንድ ነገር እንኳ እንደ ጎደልሁ ራሴን አልቆጥርም።
6Lai arī es esmu neveikls runāšanā, tad tomēr ne atziņā; to mēs jums visumā pierādījām.
6በአነጋገሬ ያልተማርሁ ብሆን እንኳ፥ በእውቀት ግን እንዲህ አይደለሁም። ነገር ግን በሰው ሁሉ መካከል በነገር ሁሉ ተገልጠንላችኋል።
7Vai tad es esmu grēkojis, sevi pazemodams, lai jūs paaugstinātu? Jo es sludināju Dieva evaņģēliju bez atlīdzības.
7ወይስ የእግዚአብሔርን ወንጌል ያለ ደመወዝ ስለ ሰበክሁላችሁ፥ እናንተ ከፍ እንድትሉ ራሴን እያዋረድሁ ኃጢአት አድርጌ ይሆንን?
8Citas draudzes es esmu izmantojis, saņemdams no tām pabalstu, lai kalpotu jums.
8እናንተን ለማገልገል ደመወዝ እየተቀበልሁ ሌሎችን አብያተ ክርስቲያናት ዘረፍሁ።
9Un kad biju pie jums un cietu trūkumu, es nevienu neapgrūtināju, bet to, kas man trūka, aizpildīja brāļi, kas man atnāca no Maķedonijas; jums es visā kalpoju un kalpošu bez apgrūtināšanas.
9ከእናንተም ጋር ሳለሁ በጎደለኝ ጊዜ፥ በማንም አልከበድሁበትም፤ ከመቄዶንያ የመጡት ወንድሞች የጎደለኝን በሙሉ ሰጥተዋልና፤ በነገርም ሁሉ እንዳልከብድባችሁ ተጠነቀቅሁ እጠነቀቅማለሁ።
10Kā Kristus patiesība manī ir, tā šo godu Ahajas apgabalā neviens man nevar atņemt.
10የክርስቶስ እውነት በእኔ እንዳለ፥ ይህ ትምክህት በእኔ ዘንድ በአካይያ አገር አይከለከልም።
11Kāpēc? Vai tāpēc, ka es jūs nemīlu? Dievs to zina!
11ስለ ምን? ስለማልወዳችሁ ነውን? እግዚአብሔር ያውቃል።
12Bet ko es daru, to arī darīšu, lai nedotu iespēju tiem, kas meklē izdevību savai lielībai, līdzināties ar mums.
12ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ ምክንያትን ከሚፈልጉቱ ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።
13Jo tādi viltus apustuļi ir viltīgi strādnieki, kas izliekas par Kristus apustuļiem.
13እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና።
14Nav arī brīnums, jo pats sātans izliekas par gaismas eņģeli!
14ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።
15Tāpēc nav nekas sevišķs, ja viņa kalpi izliekas par taisnības kalpiem; bet kādi viņu darbi, tāds būs arī gals.
15እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜአቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል።
16Es atkal saku (lai neviens netur mani par neprātīgu; bet ja jau tā, tad pieņemiet mani kā neprātīgu, lai arī es varētu mazliet palielīties).
16እንደ ገና እላለሁ። ለማንም ሰው ሞኝ የሆንሁ አይምሰለው፤ ያለዚያ ግን እኔ ደግሞ ጥቂት እመካ ዘንድ እንደ ሞኝ እንኳ ሆኜ ተቀበሉኝ።
17Ko es saku šinī dižošanās lietā, to es nesaku pēc Dieva prāta, bet it kā neprātā.
17እንደዚህ ታምኜ ስመካ የምናገረው፥ በሞኝነት እንጂ ጌታ እንዳዘዘኝ አልናገርም።
18Bet ja daudzi lielās tanī, kas attiecas uz miesu, tad arī es lielīšos.
18ብዙዎች በዓለማዊ ነገር ስለሚመኩ እኔ ደግሞ እመካለሁ።
19Jo jūs, paši prātīgi būdami, labprāt ciešat neprātīgos.
19ልባሞች ስለምትሆኑ በደስታ ሞኞችን ትታገሣላችሁና፤
20Jūs panesat, ja kāds jūs verdzina, ja kāds izmanto, ja kāds ko atņem, ja kāds lielās, ja kāds jūs sit sejā.
20ማንም ባሪያዎች ቢያደርጋችሁ፥ ማንም ቢበላችሁ፥ ማንም ቢቀማችሁ፥ ማንም ቢኮራባችሁ፥ ማንም ፊታችሁን በጥፊ ቢመታችሁ ትታገሣላችሁና።
21Sev par kaunu es saku, ka šinī ziņā mēs bijām vāji. Bet ja kāds uzdrošinās lepoties (to saku neprātā), tad uzdrošinos arī es.
21ደካሞች መስለን እንደ ነበርን በውርደት እላለሁ። ነገር ግን በሞኝነት እላለሁ፤ ማንም በሚደፍርበት እኔ ደግሞ እደፍርበታለሁ።
22Tie ir ebreji, arī es; tie ir izraēlieši, arī es; tie ir Ābrahama pēcnācēji, arī es.
22ዕብራውያን ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የእስራኤል ወገን ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የአብርሃም ዘር ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የክርስቶስ አገልጋዮች ናቸውን?
23Tie ir Kristus kalpi (es runāju kā neprātīgais), vēl vairāk es tāds esmu: daudzos darbos, vairākkārt cietumos, bezmēra šaustīšanā, bieži nāves briesmās.
23እንደ እብድ ሰው እላለሁ፤ እኔ እበልጣለሁ፤ በድካም አብዝቼ፥ በመገረፍ አብዝቼ፥ በመታሰር አትርፌ፥ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ።
24No jūdiem piecas reizes saņēmu pa četrdesmit sitienu, atskaitot vienu.
24አይሁድ አንድ ሲጎድል አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ ገረፉኝ።
25Trīs rezes tiku rīkstēm šaustīts, vienreiz akmeņiem mētāts, trīs reizes izcietu kuģa bojā eju, diennakti biju jūras dzelmē;
25ሦስት ጊዜ በበትር ተመታሁ፤ አንድ ጊዜ በድንጋይ ተወገርሁ፤ መርከቤ ሦስት ጊዜ ተሰበረ፤ ሌሊትና ቀን በባሕር ውስጥ ኖርሁ።
26Bieži biju ceļojumos, upju briesmās, laupītāju apdraudēts, briesmas man draudēja no savas tautas, briesmas no pagāniem, biju briesmās pilsētās, briesmās tuksnesī, briesmās uz jūras, briesmas draudēja no viltus brāļiem;
26ብዙ ጊዜ በመንገድ ሄድሁ፤ በወንዝ ፍርሃት፥ በወንበዴዎች ፍርሃት፥ በወገኔ በኩል ፍርሃት፥ በአሕዛብ በኩል ፍርሃት፥ በከተማ ፍርሃት፥ በምድረ በዳ ፍርሃት፥ በባሕር ፍርሃት፥ በውሸተኞች ወንድሞች በኩል ፍርሃት ነበረብኝ፤
27Darbā un pūlēs, daudz negulētās naktīs, badā un slāpēs, daudzos gavēņos, saltumā un kailumā.
27በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት፥ በራብና በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም፥ በብርድና በራቁትነት ነበርሁ።
28Bez tam vēl viss pārējais, arī ikdienas drūzma ap mani un rūpes par visām draudzēm.
28የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።
29Ja kāds ir nespēcīgs, vai es nekļūstu nespēcīgs? Ja kāds tiek ieļaunots, vai es neiedegos?
29የሚደክም ማን ነው፥ እኔም አልደክምምን? የሚሰናከል ማን ነው፥ እኔም አልናደድምን?
30Ja jau jādižojas, tad dižošos ar savu vājību.
30ትምክህት የሚያስፈልግ ከሆነ፥ ከድካሜ በሚሆነው ነገር እመካለሁ።
31Dievs un mūsu Kunga Jēzus Kristus Tēvs zina, ka es nemeloju. Viņam gods mūžīgi!
31ለዘላለም የተባረከ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት እንዳልዋሽ ያውቃል።
32Damaskā ķēniņa Aretas zemes pārvaldnieks apsargāja pilsētu, lai mani notvertu;
32በደማስቆ አርስጦስዮስ ከተባለ ንጉሥ በታች የሆነ የሕዝብ ገዥ ሊይዘኝ እየወደደ የደማስቆ ሰዎችን ከተማ ያስጠብቅ ነበር፥
33Bet caur logu grozā mani nolaida pāri mūrim, un tā es izglābos no viņu rokām.
33በቅጥሩም ባለ መስኮት በቅርጫት አወረዱኝና ከእጁ አመለጥሁ።