1Ja jau jālielās (lai gan tas nepieklājas), tad es pāriešu uz Kunga parādībām un atklāsmēm.
1ትምክህት የሚያስፈልግ ነው፤ አይጠቅምም ነገር ግን ከጌታ ወዳለው ራእይና መገለጥ እመጣለሁ።
2Kristū es pazīstu cilvēku, kas pirms četrpadsmit gadiem, nezinu, vai miesā, nezinu arī, vai ārpus miesas, Dievs to zina, tika aizrauts trešajās debesīs.
2ሰውን በክርስቶስ አውቃለሁ፥ በሥጋ እንደ ሆነ አላውቅም ወይም ከሥጋ ውጭ እንደ ሆነ አላውቅም፥ እግዚአብሔር ያውቃል፤ እንዲህ ያለው ሰው ከአሥራ አራት ዓመት በፊት እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ ተነጠቀ።
3Un es zinu, ka šis cilvēks vai miesā, vai ārpus miesas, nezinu, Dievs to zina,
3እንዲህ ያለውንም ሰው አውቃለሁ፥ በሥጋ እንደ ሆነ ወይም ያለ ሥጋ እንደ ሆነ አላውቅም፥ እግዚአብሔር ያውቃል፤
4Tika aizrauts paradīzē un dzirdēja noslēpumainus vārdus, ko cilvēks nedrīkst izrunāt.
4ወደ ገነት ተነጠቀ፥ ሰውም ሊናገር የማይገባውን የማይነገረውን ቃል ሰማ።
5Ar viņu es lielīšos, bet ar sevi es nelielīšos, kā vienīgi ar savām vājībām.
5እንደዚህ ስላለው እመካለሁ፥ ስለ ራሴ ግን ከድካሜ በቀር አልመካም።
6Ja arī es gribēšu dižoties, es nebūšu neprātīgs, jo es teikšu patiesību; bet es atturos, lai kāds par mani nedomātu vairāk par to, ko tas manī saskata un ko no manis dzird.
6ልመካ ብወድስ ሞኝ አልሆንም፥ እውነትን እላለሁና፤ ነገር ግን ማንም ከሚያይ ከእኔም ከሚሰማ የምበልጥ አድርጎ እንዳይቆጥረኝ ትቼአለሁ።
7Bet lai atklāsmju daudzums mani neizceltu, manā miesā ir dots dzelonis, sātana eņģelis, kas mani pļaukā.
7ስለዚህም በመገለጥ ታላቅነት እንዳልታበይ የሥጋዬ መውጊያ፥ እርሱም የሚጎስመኝ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ፤ ይኸውም እንዳልታበይ ነው።
8Tāpēc es trīs reizes lūdzu Kungu, lai tas no manis atkāptos.
8ስለዚህ ነገር ከእኔ እንዲለይ ሦስት ጊዜ ጌታን ለመንሁ።
9Un Viņš man sacīja: Tev pietiek manas žēlastības, jo spēks nespēkā kļūst pilnīgs. Tāpēc es labprāt dižošos savā nespēkā, lai Kristus spēks mājotu manī.
9እርሱም። ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ።
10Kristus dēļ man patīk manas vājības, nievāšanas, posts, vajāšanas, apspiešana; jo, būdams nespēcīgs, es esmu spēcīgs.
10ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና።
11Es esmu kļuvis neprātīgs; jūs mani pie tā novedāt. Jums gan vajadzēja mani ieteikt, jo es nemaz neesmu zemāks par tiem, kas ir dižapustuļi, kaut gan nekas neesmu.
11በመመካቴ ሞኝ ሆኜአለሁ፤ እናንተ ግድ አላችሁኝ፤ እናንተ እኔን ልታመሰግኑ ይገባ ነበርና። እኔ ምንም ባልሆን እንኳ፥ ከዋነኞቹ ሐዋርያት በምንም አልጎድልምና።
12Tomēr manas apustuliskās sūtības pazīmes jums ir pierādītas pacietībā, zīmēs, brīnumos un spēkā.
12በእርግጥ የሐዋርያነት ምልክት በመካከላችሁ በምልክትና በድንቅ ነገር በተአምራትም በሁሉ ትዕግሥት ተደረገ።
13Un kas būtu tas, ko jūs būtu mazāk par citām draudzēm saņēmuši, ja ne tas, ka es jūs neapgrūtināju? Piedodiet man šo netaisnību!
13እኔ ራሴ ካልከበድሁባችሁ ከዚህ በቀር፥ ከሌላ ቤተ ክርስቲያን ያነሳችሁበት በምን እኮ ነው? ይህን በደሌን ይቅር በሉልኝ።
14Lūk, trešo reiz es esmu gatavs pie jums iet un neapgrūtināšu jūs; jo es nemeklēju to, kas jums ir, bet jūs pašus. Jo nav vajadzīgs, ka bērni krātu mantu vecākiem, bet vecāki bērniem.
14እነሆ፥ ወደ እናንተ እመጣ ዘንድ ስዘጋጅ ይህ ሦስተኛዬ ነው፤ አልከብድባችሁምም፥ እናንተን እንጂ ያላችሁን አልፈልግምና። ወላጆች ለልጆች እንጂ ልጆች ለወላጆች ገንዘብ ሊያከማቹ አይገባቸውምና።
15Un par jūsu dvēselēm es ļoti labprāt uzupurēšu visu, arī pats sevi uzupurēšu, lai gan, jo vairāk es jūs mīlu, pats tieku mazāk mīlēts.
15እኔ ግን ስለ ነፍሳችሁ በብዙ ደስታ ገንዘቤን እከፍላለሁ፥ ራሴን እንኳ እከፍላለሁ። ከመጠን ይልቅ ብወዳችሁ በዚህ ልክ ፍቅራችሁ የሚያንስ ነውን?
16Bet lai! Apgrūtinājis es jūs neesmu, bet es, būdams veikls, esot ieguvis jūs ar viltu.
16ይሁን እንጂ እኔ አልከበድሁባችሁም፤ ነገር ግን ሸንጋይ ሆኜ በተንኰል ያዝኋችሁ።
17Vai caur tiem, kurus pie jums sūtīju, esmu jūs piemānījis?
17ወደ እናንተ ከላክኋቸው በአንዱ ስንኳ አታለልኋችሁን?
18Es lūdzu Titu un sūtīju viņam līdz brāli. Vai Tits jūs piemānīja? Vai mēs nedarbojāmies vienā un tanī pat garā, tanīs pat pēdās?
18ቲቶን መከርሁት ከእርሱም ጋር ወንድሙን ላክሁት፤ ቲቶስ አታለላችሁን? በአንድ መንፈስ አልተመላለስንምን? በአንድ ፍለጋስ አልተመላለስንም?
19Jūs, laikam, sen jau domājat, ka mēs attaisnojamies jūsu priekšā? Mēs runājam Dieva priekšā Kristus vārdā. Vismīļie, tas viss jūsu pamācīšanai!
19ለእናንተ ስለ ራሳችን እንድንመልስ ሁልጊዜ ይመስላችኋልን? በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን፤ ነገር ግን፥ ወዳጆች፥ እናንተን ልናንጻችሁ ሁሉን እንናገራለን።
20Es baidos, lai atnācis neatrastu jūs tādus, kādus es nevēlos; un ka jūs neatrastu mani tādu, kādu jūs nevēlaties; lai nebūtu starp jums ķildu, skaudības, dusmu, ienaida, goda laupīšanas, mēlnesības, uzpūtības, nekārtības.
20ስመጣ፥ እንደምወደው ሳትሆኑ አገኛችሁ ይሆናል እኔም እንደምትወዱት ሳልሆን ታገኙኝ ይሆናል ብዬ እፈራለሁና፤ ምናልባት ክርክር ቅንዓትም ቁጣም አድመኝነትም ሐሜትም ማሾክሾክም ኩራትም ሁከትም ይሆናሉ፤
21Un kad atkal atnākšu, lai Dievs mani nepazemo jūsu priekšā un lai man nebūtu par daudziem jāskumst, kas agrāk grēkojuši, bet nav gandarījuši par nešķīstību un bezkaunību, un izlaidību, ko tie darījuši.
21እንደ ገና ስመጣ በእናንተ ዘንድ አምላኬ እንዲያዋርደኝ፥ አስቀድመውም ኃጢአት ከሠሩትና ስላደረጉት ርኵሰትና ዝሙት መዳራትም ንስሐ ካልገቡት ወገን ስለ ብዙዎች ምናልባት አዝናለሁ ብዬ እፈራለሁ።