Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

2 Corinthians

13

1Lūk, trešo reiz es nāku pie jums. Ikviena lieta tiks izšķirta, diviem vai trim lieciniekiem liecinot.
1ወደ እናንተ ስመጣ ይህ ሦስተኛዬ ነው፤ ሁሉ ነገር በሁለትና በሦስት ምስክር አፍ ይጸናል።
2Pie jums būdams, es sacīju un tagad prombūtnē saku tiem, kas agrāk grēkojuši, un visiem pārējiem, ka nesaudzēšu tos, kad atkal atnākšu.
2ሁለተኛ በእናንተ ዘንድ በነበርሁ ጊዜ እንደ ተናገርሁ አሁንም ደግሞ በሩቅ ስሆን፥ ክርስቶስ በእኔ አድሮ እንዲናገር ማስረጃ ከፈለጋችሁ፥ እንደ ገና ብመጣ እንዳልራራላቸው አስቀድመው ኃጢአት ላደረጉት ለሌሎችም ሁሉ አስቀድሜ ብዬአለሁ፥ አስቀድሜም እላለሁ። ክርስቶስም ስለ እናንተ አይደክምም ነገር ግን በእናንተ ኃይለኛ ነው።
3Vai jūs meklējat pierādījumu tam, ka manī runā Kristus? Viņš jūsos nav bezspēcīgs, bet Viņš jūsos varens.
4በድካም ተሰቅሎአልና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ኃይል በሕይወት ይኖራል። እኛ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንደክማለንና፥ ነገር ግን ስለ እናንተ በሆነ በእግዚአብሔር ኃይል ከእርሱ ጋር በሕይወት እንኖራለን።
4Lai gan Viņš krustā sists nespēkā, bet dzīvo Dieva spēkā. Arī mēs Viņā esam nespēcīgi, bet mēs dzīvosim starp jums līdz ar Viņu Dieva spēkā.
5በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን?
5Pārbaudiet paši sevi, vai esat ticīgi, pārbaudiet sevi! Vai jūs sevī neatzīstat, ka Kristus ir jūsos? Ja nē, tad jūs esat neuzticīgi.
6እኛ ግን የማንበቃ እንዳይደለን ልታውቁ ተስፋ አደርጋለሁ።
6Bet es ceru, ka jūs atzīsiet, ka mēs esam uzticīgi.
7ክፉ ነገርንም ከቶ እንዳታደርጉ ወደ እግዚአብሔር እንጸልያለን፤ እኛ የምንበቃ ሆነን እንገለጥ ዘንድ አይደለም ነገር ግን እኛ ምንም እንደማንበቃ ብንሆን፥ እናንተ መልካሙን ታደርጉ ዘንድ ነው።
7Un mēs lūdzam Dievu, lai jūs nedarītu nekā ļauna ne tāpēc, lai mūs uzskatītu par uzticīgiem, bet lai jūs darītu labu un mēs būtu it kā nederīgi.
8ለእውነት እንጂ በእውነት ላይ ምንም ለማድረግ አንችልምና።
8Jo mēs nekā nespējam pret patiesību, bet par patiesību.
9እኛ ስንደክም እናንተም ኃይለኞች ስትሆኑ ደስ ብሎናልና፤ እናንተ ፍጹማን ትሆኑ ዘንድ ለዚህ ደግሞ እንጸልያለን።
9Mēs priecājamies, ka mēs esam vāji, bet jūs stipri. To arī izlūdzamies, lai jūs būtu pilnīgi.
10ስለዚህ ጌታ ለማፍረስ ያይደለ ለማነጽ እንደ ሰጠኝ ሥልጣን፥ ከእናንተ ጋር ሳለሁ በቁርጥ እንዳልሠራ በሩቅ ሆኜ ይህን እጽፋለሁ።
10Tāpēc es jums šo rakstu prombūtnē, lai, pie jums esot, man nevajadzētu bargāk rīkoties saskaņā ar to varu, ko Kungs man devis celšanai, bet ne graušanai.
11በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ደኅና ሁኑ። ፍጹማን ሁኑ፥ ምክሬን ስሙ፥ በአንድ ልብ ሁኑ፥ በሰላም ኑሩ፥ የፍቅርና የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል።
11Bez tam, brāļi, esiet līksmi, topiet pilnīgi, ieprieciniet viens otru, esiet vienprātīgi, uzturiet mieru: un miera un mīlestības Dievs būs ar jums.
12በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ።
12Sveiciniet viens otru ar svētu skūpstu! Visi svētie jūs sveicina.
13ቅዱሳን ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
13Mūsu Kunga Jēzus Kristus žēlastība un Dieva mīlestība, un Svētā Gara sadraudzība lai ir ar jums visiem! Amen.
14የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።