1Kad mūsu šīs dzīves laicīgais miteklis būs nojaukts, mēs zinām, ka mums no Dieva ir mūžīgs mājoklis debesīs, kas nav rokām celts.
1ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና።
2Jo šinī mēs nopūšamies, ilgodamies būt ietērpti tanī mājoklī, kas ir no debesīm,
2በዚህ ውስጥ በእውነት እንቃትታለንና፥
3Un, ja būsim ietērpti, nebūsim kaili.
3ከሰማይም የሚሆነውን መኖሪያችንን እንድንለብስ እንናፍቃለንና ለብሰን ራቁታችንን አንገኝም።
4Jo mēs, šinī teltī būdami, apgrūtināti nopūšamies, negribēdami, lai mūs izģērbj, bet lai pārģērbj, dzīvei aprijot mirstīgo.
4በእውነትም የሚሞተው በሕይወት ይዋጥ ዘንድ ልንለብስ እንጂ ልንገፈፍ የማንወድ ስለ ሆነ፥ በድንኳኑ ያለን እኛ ከብዶን እንቃትታለን።
5Bet Dievs ir tas, kas mūs tam sagatavojis un devis Garu ķīlā.
5ነገር ግን ለዚሁ የሠራን እግዚአብሔር ነው እርሱም የመንፈሱን መያዣ ሰጠን።
6Tāpēc mums vienmēr ir stipra pārliecība un zinām, ka mēs, kamēr esam šinī miesā, no Kunga esam tālu,
6እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥
7(Jo mēs vēl dzīvojam ticībā, bet ne redzēšanā.)
8ታምነናል ይልቁንም ከሥጋ ተለይተን በስደት መኖር በጌታም ዘንድ ማደር ደስ ይለናል።
8Bet mums ir vēlēšanās un stipra griba labāk aiziet no šīs miesas un būt Kunga klātbūtnē.
9ስለዚህ ደግሞ ብናድር ወይም ተለይተን ብንሆን እርሱን ደስ የምናሰኝ ልንሆን እንቀናለን።
9Un tāpēc mes cenšamies vai nu prombūtnē, vai klātbūtnē Viņam būt patīkami.
10መልካም ቢሆን ወይም ክፉ እንዳደረገ፥ እያንዳንዱ በሥጋው የተሠራውን በብድራት ይቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና።
10Jo mums visiem jāstājas Kristus soģa krēsla priekšā, lai katrs saņemtu attiecīgi tam, ko viņš, būdams savā miesā, labu vai ļaunu darījis.
11እንግዲህ የጌታን ፍርሃት አውቀን ሰዎችን እናስረዳለን ለእግዚአብሔር ግን የተገለጥን ነን፤ በሕሊናችሁም ደግሞ የተገለጥን እንደ ሆንን ተስፋ አደርጋለሁ።
11Tātad, pazīdami bijību pret Kungu, mēs pārliecinām cilvēkus. Bet Dievs mūs pazīst, un es ceru, ka arī jūsu sirdsapziņas mūs pazīst.
12በመልክ እንጂ በልብ ለማይመኩ የምትመልሱላቸው መልስ እንዲኖራችሁ፥ በእኛ ልትመኩ ምክንያት እንሰጣችኋለን እንጂ ራሳችንን ደግሞ ለእናንተ የምናመሰግን አይደለንም።
12Mēs jums sevi atkal neieteicam, bet jums dodam iemeslu ar mums lepoties, lai jūs varētu atbildēt tiem, kas lielās ar ārišķīgo, bet ne ar to, kas sirdī.
13እብዶች ብንሆን፥ ለእግዚአብሔር ነው፤ ባለ አእምሮዎች ብንሆን፥ ለእናንተ ነው።
13Ja aizraujamies līdz neprātam, tas Dievam; ja rīkojamies apdomīgi, tas jūsu labā.
14ይህን ስለቆረጥን የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናልና፤ አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፤ እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤
14Jo Kristus mīlestība mūs skubina, kad apdomājam to: ja viens miris par visiem, tad mēs visi ir miruši.
15በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ።
15Bet par visiem mira Kristus, lai tie, kas dzīvo, nedzīvo vairs sev, bet Tam, kas par viņiem miris un augšāmcēlies.
16ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም።
16Tāpēc no šī brīža mēs neviena nepazīstam miesīgi; un ja mēs Kristu esam pazinuši miesīgi, tad tagad vairs tā nepazīstam.
17ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።
17Tātad, ja kas ir Kristū, tas ir jauns radījums; vecais ir pagājis; lūk, viss kļuvis jauns.
18ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤
18Bet viss no Dieva, kas mūs samierināja ar sevi caur Kristu un deva mums samierināšanās kalpošanu.
19እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።
19Jo Dievs caur Kristu samierināja pasauli ar sevi, nepieskaitīdams tiem viņu grēkus un ielikdams mūsos samierināšanās vārdu.
20እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን።
20Kristus vietā mēs izpildām sūtību, it kā Dievs pamācītu caur mums. Kristus vietā mēs jūs lūdzam: samierinieties ar Dievu!
21እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።
21To, kas grēka nepazina, Viņš mūsu dēļ padarīja par grēku, lai mēs caur Viņu kļūtu Dieva taisnība.