1Būdami jūsu līdzstrādnieki, mēs atgādinām, lai jūs nesaņemtu Dieva žēlastību veltīgi.
1አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤
2Jo Viņš saka: žēlastības laikā es tevi paklausīju un pestīšanas dienā es tev palīdzēju. Lūk, tagad ir žēlastības laiks, lūk, tagad pestīšanas diena.
2በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።
3Mēs nevienam nekādu apgrēcību nedodam, lai mūsu kalpošana netiktu nopelta;
3አገልግሎታችንም እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም።
4Bet ka visā esam Dieva kalpi, mēs pierādām lielā pacietībā, bēdās, trūkumā un bailēs,
4ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤
5Šaustīšanā, cietumos, uztraukumos, darbā, negulēšanā, gavēnī,
5በብዙ መጽናት፥ በመከራ፥ በችግር፥ በጭንቀት፥ በመገረፍ፥ በወኅኒ፥ በሁከት፥ በድካም፥ እንቅልፍ በማጣት፥
6Šķīstībā, zināšanā, lēnprātībā, laipnībā, Svētajā Garā, neviltotā mīlestībā,
6በመጦም፥ በንጽህና፥ በእውቀት፥ በትዕግሥት፥ በቸርነት፥ በመንፈስ ቅዱስ፥ ግብዝነት በሌለው ፍቅር፥ በእውነት ቃል፥
7Patiesības vārdā, Dieva spēkā, ar taisnības ieročiem pa labi un pa kreisi,
7በእግዚአብሔር ኃይል፥ ለቀኝና ለግራ በሚሆን በጽድቅ የጦር ዕቃ፥ በክብርና በውርደት፥
8Ar godu un negodu, ar neslavu un labu slavu, it kā viltnieki un tomēr patiesīgi; kā nepazīstami un tomēr zināmi;
8በክፉ ወሬና በመልካም ወሬ ራሳችንን እናማጥናለን፤ አሳቾች ስንባል እውነተኞች ነን፤
9Kā mirēji, un, lūk, mēs dzīvojam; kā šaustīti, bet nenonāvēti;
9ያልታወቁ ስንባል የታወቅን ነን፤ የምንሞት ስንመስል እነሆ ሕያዋን ነን፤ የተቀጣን ስንሆን አንገደልም፤
10Kā noskumuši, bet vienmēr priecīgī; kā trūkumcietēji, bet kas daudzus dara bagātus; kā tādi, kam nekā nav un tomēr ir viss.
10ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው።
11Korintieši, mēs jums atklāti sakām, mūsu sirds ir plaši atvērt.
11እናንተ የቆሮንቶስ ሰዎች ሆይ፥ አፋችን ለእናንተ ተከፍቶአል ልባችንም ሰፍቶላችኋል፤
12Mēs pret jums neesam šaursirdīgi, bet jūs pret mums esat šaursirdīgi.
12በእኛ አልጠበባችሁም በሆዳችሁ ግን ጠቦባችኋል፤
13Tā kā jūs saņemat to pašu algu, es kā bērniem jums saku: kļūstiet arī jūs atvērtāki!
13ልጆቼ እንደ መሆናችሁ ግን እላችኋለሁ፥ እናንተ ደግሞ ብድራት መልሳችሁልን ተስፋፉ።
14Nevelciet jūgu kopā ar neticīgajiem, jo kas kopējs ir taisnībai ar netaisnību? Vai kāda sadraudzība gaismai ar tumsu?
14ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?
15Bet kāda saskaņa Kristum ar Beliālu? Vai kāda daļa ir ticīgajam ar neticīgo?
15ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?
16Bet kā sader Dieva svētnīca ar elkiem? Jo jūs esat dzīvā Dieva svētnīca, kā Dievs to saka: es viņos mājošu un starp viņiem staigāšu, un es būšu viņu Dievs, un viņi būs mana tauta.
16ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስም ከጣዖት ጋር ምን መጋጠም አለው? እኛ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነንና እንዲሁም እግዚአብሔር ተናገረ እንዲህ ሲል። በእነርሱ እኖራለሁ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፥ አምላካቸውም እሆናለሁ እነርሱም ሕዝቤ ይሆናሉ።
17Tāpēc aizejiet no viņu vidus un nošķirieties, saka Kungs, un netīram nepieskarieties!
17ስለዚህም ጌታ። ከመካከላቸው ውጡና የተለያችሁ ሁኑ ርኵስንም አትንኩ ይላል፤ ሁሉንም የሚገዛ ጌታ። እኔም እቀበላችኋለሁ፥ ለእናንተም አባት እሆናለሁ እናንተም ለእኔ ወንድ ልጆችና ሴት ልጆች ትሆናላችሁ ይላል።
18Un es jūs pieņemšu, un es būšu jums Tēvs, un jūs būsiet mani dēli un meitas, saka visspēcīgais Kungs.