1Vismīļie, tā kā mums ir tādi apsolījumi, tīrīsimies no katra miesas un gara traipa un Dieva bijībā sekmēsim savu svēttapšanu!
1እንግዲህ፥ ወዳጆች ሆይ፥ የዚህ ተስፋ ቃል ካለን፥ በእግዚአብሔር ፍርሃት ቅድስናን ፍጹም እያደረግን ሥጋንና መንፈስን ከሚያረክስ ሁሉ ራሳችንን እናንጻ።
2Pieņemiet mūs! Mēs nevienam neesam netaisnību nodarījuši, nevienu notiesājuši, nevienu apgājuši.
2በልባችሁ ስፍራ አስፉልን፤ ማንንም አልበደልንም፥ ማንንም አላጠፋንም፥ ማንንም አላታለልንም።
3Ne jūsu notiesāšanai es to saku, jo es jau agrāk teicu, ka jūs esat mūsu sirdīs, lai kopā mirtu un kopā dzīvotu.
3ለኵነኔ አልልም፤ በአንድነት ለመሞትና በአንድነት ለመኖር በልባችን እንዳላችሁ አስቀድሜ ብዬአለሁና።
4Es pilnīgi paļaujos uz jums, es esmu ļoti lepns uz jums. Iepriecinājuma pilns, es pārpilnībā izjūtu prieku visās mūsu bēdās.
4ስለ እናንተ እምነቴ ታላቅ ነው፥ በእናንተ ምክንያት ትምክህቴ ታላቅ ነው፤ መጽናናት ሞልቶብኛል፤ በመከራችን ሁሉ ደስታዬ ከመጠን ይልቅ ይበዛል።
5Jo, kad nonācām Maķedonijā, mūsu miesai nebija nekāda miera, bet izcietām visādas bēdas: no ārienes uzbrukumus, iekšienē bailes.
5ወደ መቄዶንያም በመጣን ጊዜ፥ በሁሉ ነገር መከራን ተቀበልን እንጂ ሥጋችን ዕረፍት አልነበረውም፤ በውጭ ጠብ ነበረ፥ በውስጥ ፍርሃት ነበረ።
6Bet Dievs, kas iepriecina pazemīgos, Titam atnākot, iepriecināja arī mūs.
6ነገር ግን ኀዘንተኞችን የሚያጽናና አምላክ በቲቶ መምጣት አጽናናን፤
7Bet nevien viņa atnākšana, bet arī iepriecinājums ar kādu jūs viņu iepriecinājāt, jo viņš mums stāstīja par jūsu rūpēm par mani, tā ka es vēl vairāk priecājos.
7በመምጣቱም ብቻ አይደለም ነገር ግን ናፍቆታችሁንና ልቅሶአችሁን ስለ እኔም ቅንዓታችሁን ሲናገረን በእናንተ ላይ በተጽናናበት መጽናናት ደግሞ ነው፤ ስለዚህም ከፊት ይልቅ ደስ አለን።
8Es nenožēloju, ka es jūs apbēdināju ar savu vēstuli. Ja man arī bija žēl, redzot, ka tā vēstule (kaut vai uz brīdi) jūs apbēdinājusi,
8በመልእክቴ ያሳዘንኋችሁ ብሆን እንኳ አልጸጸትም፤ የተጸጸትሁ ብሆን እንኳ፥ ያ መልእክት ጥቂት ጊዜ ብቻ እንዳሳዘናችሁ አያለሁና አሁን ለንስሐ ስላዘናችሁ ደስ ብሎኛል እንጂ ስላዘናችሁ አይደለም፤
9Tad tagad es priecājos ne tāpēc, ka jūs bijāt noskumuši, bet tāpēc, ka noskumāt, lai gandarītu; jo jūs noskumāt pēc Dieva prāta, lai jūs mūsu dēļ nekādā ziņā neciestu zaudējumu.
9በምንም ከእኛ የተነሣ እንዳትጎዱ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ አዝናችኋልና።
10Jo Dievam patīkamas skumjas rada noteiktu gandarījumu pestīšanai, bet pasaulīgās skumjas nes nāvi.
10እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን ጸጸት የሌለበትን፥ ወደ መዳንም የሚያደርሰውን ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ኀዘን ግን ሞትን ያመጣል።
11Jo, lūk, tās pašas Dievam patīkamās skumjas, ar kādām es jūs apbēdināju, kādu rūpību tās jūsos radījušas, arī aizstāvēšanos, arī īgnumu, arī bailes, arī ilgas, arī centību, arī nosodīšanu! Katrā ziņā jūs pierādījāt, ka jūs šinī lietā neesat vainojami.
11እነሆ፥ ይህ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን እንዴት ያለ ትጋት፥ እንዴት ያለ መልስ፥ እንዴት ያለ ቁጣ፥ እንዴት ያለ ፍርሃት፥ እንዴት ያለ ናፍቆት፥ እንዴት ያለ ቅንዓት፥ እንዴት ያለ በቀል በመካከላችሁ አደረገ። በዚህ ነገር ንጹሐን እንደ ሆናችሁ በሁሉ አስረድታችኋል።
12Tātad, ja es jums rakstīju, tad ne tā dēļ, kas padarīja netaisnību, un arī ne cietēja dēļ, bet lai parādītu tās rūpes, kas mums ir jūsu labā
12እንግዲያስ የጻፍሁላችሁ ብሆን እንኳ፥ ስለ እኛ ያላችሁ ትጋታችሁ ከእናንተ ዘንድ በእግዚአብሔር ፊት እንዲገለጥ እንጂ፥ ስለ በዳዩ ወይም ስለ ተበዳዩ አልጻፍሁም። ስለዚህ ተጽናንተናል።
13Dieva priekšā. Tāpēc mēs esam apmierināti. Bet mūsu apmierinājumā mēs vēl vairāk priecājamies par Tita prieku, jo jūs visi atspirdzinājāt viņa garu.
13በመጽናናታችንም ስለ ቲቶ ደስታ አብልጦ ደስ አለን፥ መንፈሱ በሁላችሁ ዐርፎአልና፤
14Un ja es jūs kaut kā viņam esmu cildinājis, tad neesmu palicis kaunā, bet kā viss, ko jums runājām, ir patiesība, tā arī mūsu cildināšana Titam ir bijusi patiesība;
14ለእርሱ በምንም ስለ እናንተ የተመካሁ እንደ ሆነ አላፈርሁምና፥ ነገር ግን ሁሉን ለእናንተ በእውነት እንደ ተናገርን፥ እንደዚህ ደግሞ ትምክህታችን በቲቶ ፊት እውነት ሆነ።
15Un, atminoties visu jūsu paklausību, viņa sirds vēl vairāk ir jums pievērsusies, jo jūs viņu uzņēmāt bijībā un bailēs.
15ስለዚህም በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ እንዴት እንደተቀበላችሁት፥ የሁላችሁን መታዘዝ እያሰበ ፍቅሩ በእናንተ ላይ እጅግ በዝቶአል።
16Es priecājos, ka es visā varu uz jums paļauties.
16በነገር ሁሉ ተማምኜባችኋለሁና ደስ ይለኛል።