1Bet mēs jums, brāļi, ziņojam par Dieva žēlastību, kas dota Maķedonijas draudzēm.
1ወንድሞች ሆይ፥ ለመቄዶንያ አብያተ ክርስቲያናት የተሰጠውን የእግዚአብሔርን ጸጋ እናስታውቃችኋለን፤
2Jo viņiem, lai gan daudz bēdu pārbaudītiem, prieks bija pārpilnībā; un viņi, paši dzīvodami lielā trūkumā, bija ļoti bagāti savā sirsnībā.
2በብዙ መከራ ተፈትነው ሳሉ የደስታቸው ብዛትና የድህነታቸው ጥልቅነት የልግስናቸውን ባለ ጠግነት አብዝቶአል፤
3Es apliecinu par viņiem, ka tie attiecīgi savām spējām un pat pāri spējām bijuši labvēlīgi.
3እንደ ዓቅማቸው መጠን ከዓቅማቸውም የሚያልፍ እንኳ ወደው እንደ ሰጡ እመሰክርላቸዋለሁና።
4Mūs pierunādami, viņi ļoti lūdza mūsu atļauju piedalīties svēto pabalstīšanā.
4ለቅዱሳን በሆነው አገልግሎት እንዲተባበሩ ይህን ቸርነት በብዙ ልመና ከእኛ ይለምኑ ነበር፥
5Un pāri mūsu cerībām viņi vispirms ziedoja sevi Kungam un tad mums saskaņā ar Dieva prātu.
5አስቀድመውም በእግዚአብሔር ፈቃድ ራሳቸውን ለጌታ ለእኛም ሰጡ እንጂ እንዳሰብን አይደለም።
6Tad mēs lūdzām Titu: kā viņš iesācis, tā lai arī pabeidz pie jums šo mīlestības darbu.
6ስለዚህም ቲቶ አስቀድሞ እንደ ጀመረ እንዲሁ ደግሞ ይህን ቸር ሥራ ደግሞ በእናንተ ዘንድ ሊፈጽም ለመንን።
7Bet tā kā jūs visā esat bagāti: gan ticībā, gan vārdos, gan zināšanā, gan visādos centienos un klāt vēl jūsu mīlestībā iepretim mums, tad esiet bagāti arī šinī mīlestības darbā!
7ነገር ግን በነገር ሁሉ፥ በእምነትና በቃል በእውቀትም በትጋትም ሁሉ ለእኛም በፍቅራችሁ እንደ ተረፋችሁ፥ በዚህ ቸር ሥራ ደግሞ ትረፉ።
8To es nesaku pavēlēdams, bet, ievērojot citu centību, pārbaudu jūsu mīlestības īstenību.
8ትእዛዝ እንደምሰጥ አልልም፥ ነገር ግን በሌሎች ትጋት በኩል የፍቅራችሁን እውነተኛነት ደግሞ ልመረምር እላለሁ፤
9Jo jūs zināt mūsu Kunga Jēzus Kristus žēlastību, ka Viņš, būdams bagāts, jūsu dēļ kļuvis nabags, lai Viņa nabadzībā jūs kļūtu bagāti.
9የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።
10Šinī gadījumā es dodu šādu padomu: tas jums derīgi, ka jūs pagājušā gadā iesākāt nevien ar darbu, bet arī ar labu gribu.
10በዚህም ነገር ምክር እሰጣለሁ፤ ከአምና ጀምራችሁ ለማድረግ ብቻ ያይደለ ነገር ግን ለማሰብ ደግሞ አስቀድማችሁ የጀመራችሁት ይህ ይጠቅማችኋልና፤
11Bet tagad izpildiet to arī darbā, lai labprātīgai gribai seko arī izpildīšana no tā, kas jums ir!
11አሁንም ለማሰብ በጎ ፈቃድ እንደ ነበረ፥ እንዲሁ እንዳላችሁ መጠን መፈጸም ደግሞ ይሆን ዘንድ፥ ማድረጉን ደግሞ ፈጽሙ።
12Ja laba griba ir, tad tā labpatīkama tanī, kas ir, bet ne no tā, kā nav.
12በጎ ፈቃድ ቢኖር፥ እንዳለው መጠን የተወደደ ይሆናል እንጂ እንደሌለው መጠን አይደለም።
13Jo nedrīkst būt, ka citu atvieglošana jūs novestu trūkumā; te jābūt vienlīdzībai.
13ለሌሎች ዕረፍት ለእናንተም መከራ እንዲሆን አይደለም፥ ትክክል እንዲሆን ነው እንጂ፤
14Tagadējā laikā jūsu pārpilnība lai palīdz viņu trūkumam, un viņu pārpilnība lai aizpilda jūsu trūkumu, lai būtu vienlīdzība, kā ir rakstīts:
14የእነርሱ ትርፍ ደግሞ የእናንተን ጉድለት እንዲሞላ በአሁኑ ጊዜ የእናንተ ትርፍ የእነርሱን ጉድለት ይሙላ፤ በትክክል እንዲሆን፥ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ።
15Kam bija daudz, tam nebija pārpilnības; kam bija maz, tas necieta trūkumu.
15ብዙ ያከማቸ አላተረፈም፥ ጥቂትም ያከማቸ አላጎደለም።
16Bet lai pateicība Dievam, kas Titam sirdī devis tādu pat rūpību par jums.
16ነገር ግን በቲቶ ልብ ስለ እናንተ ያንን ትጋት የሰጠ አምላክ ይመስገን፤
17Jo viņš, pieņēmis manu uzaicinājumu un būdams centības pilns, labprātīgi aizceļoja pie jums.
17ምክራችንን ተቀብሎአልና፥ ትጋት ግን ስለ በዛበት ወዶ ወደ እናንተ ይወጣል።
18Reizē ar viņu mēs nosūtījām brāli, kā gods evaņģēlija sludināšanā izpaudies visās draudzēs.
18ከእርሱም ጋር ስለ ወንጌል ስብከት በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የተመሰገነውን ወንድም እንልካለን፤
19Un nevien tas, bet draudzes viņu iecēlušas par mūsu ceļojuma pavadoni šinī mīlestības darbā, ko mēs strādājam Kunga godam un mūsu labās gribas pierādīšanai.
19ይህም ብቻ አይደለም ነገር ግን የጌታን የራሱን ክብርና የእኛን በጎ ፈቃድ ለማሳየት በምናገለግለው በዚህ ቸር ሥራ ከእኛ ጋር እንዲጓደድ በአብያተ ክርስቲያናት ደግሞ ተመረጠ።
20Tā mēs izvairāmies, lai kāds mūs nenopeltu bagātīgo dāvanu dēļ, ko esam savākuši;
20ስለምናገለግለው ስለዚህ ለጋስ ስጦታ ማንም እንዳይነቅፈን እንጠነቀቃለን፤
21Jo mēs rūpējamies nevien par to, kas labs Dievam, bet arī cilvēkiem.
21በጌታ ፊት ብቻ ያይደለ ነገር ግን በሰው ፊት ደግሞ መልካም የሆነውን እናስባለንና።
22Viņiem līdz mēs nosūtījām mūsu brāli, kura centību mēs bieži daudzos gadījumos esam pārbaudījuši; tagad, pilnīgi paļaudamies uz jums, viņš kļuvis vēl centīgāks.
22ብዙ ጊዜም በብዙ ነገር መርምረን ትጉ እንደ ሆነ ያገኘነውን፥ አሁንም በእናንተ እጅግ ስለሚታመን ከፊት ይልቅ እጅግ ትጉ የሚሆነውን ወንድማችንን ከእነርሱ ጋር እንልካለን።
23Kas attiecas uz Titu, tad viņš ir mans līdzgaitnieks un līdzstrādnieks jūsu labā; kas attiecas uz mūsu brāļiem, tad viņi ir draudžu sūtņi un Kristus gods.
23ስለ ቲቶ የሚጠይቅ ቢኖር ስለ እናንተ አብሮኝ የሚሠራ ባልንጀራዬ ነው፤ ስለ ወንድሞቻችን የሚጠይቅ ቢኖርም የአብያተ ክርስቲያናት መልእክተኞችና የክርስቶስ ክብር ናቸው።
24Tātad parādiet viņiem savu mīlestību un attaisnojiet mūsu labo atsauksmi par jums visu draudžu priekšā!
24እንግዲህ የፍቅራችሁንና ስለ እናንተ ያለውን የትምክህታችንን መግለጫ በአብያተ ክርስቲያናት ፊት ለእነርሱ ግለጡ።