1Kad Vasarsvētku diena bija pienākusi, visi viņi bija kopā tanī pat vietā.
1በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥
2Un piepeši no debesīm nāca rūkoņa, it kā stipra vēja pūsma, un piepildīja visu māju, kur tie sēdēja.
2ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው።
3Un viņiem parādījās mēles it kā no uguns, kas sadalījās un nolaidās uz ikviena no viņiem.
3እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው።
4Un visi tika Svētā Gara piepildīti un iesāka runāt dažādās valodās, kā Svētais Gars deva viņiem izrunāt.
4በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።
5Bet Jeruzalemē dzīvoja jūdi, dievbijīgi vīri no visām tautām zem debess.
5ከሰማይም በታች ካሉ ሕዝብ ሁሉ በጸሎት የተጉ አይሁድ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፤
6Kad šī balss atskanēja, daudzi sanāca kopā un apjuka, jo ikviens dzirdēja tos runājam savā valodā.
6ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ።
7Un visi samulsa un brīnījās, sacīdami: Lūk, vai tie visi, kas runā, nav galilejieši?
7ተገርመውም ተደንቀውም እንዲህ አሉ። እነሆ፥ እነዚህ የሚናገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን?
8Un kā mēs ikviens dzirdējām savu valodu, kurā mēs dzimuši?
8እኛም እያንዳንዳችን የተወለድንበትን የገዛ ቋንቋችንን እንዴት እንሰማለን?
9Partieši un mēdieši, un elamitieši, un kas dzīvo Mezopotāmijā, Jūdejā un Kapadokijā, Pontā un Āzijā.
9የጳርቴና የሜድ የኢላሜጤም ሰዎች፥ በሁለት ወንዝም መካከል በይሁዳም በቀጰዶቅያም በጳንጦስም በእስያም፥
10Frīģijā un Pamfīlijā, Ēģiptē un Lībijas daļā ap Kirēni un ienācēji no Romas,
10በፍርግያም በጵንፍልያም በግብፅም በቀሬናም በኩል ባሉት በሊቢያ ወረዳዎች የምንኖር፥ በሮሜም የምንቀመጥ፥ አይሁድም ወደ ይሁዲነትም የገባን፥
11Tāpat jūdi un prozelīti, krētieši un arābi; mēs dzirdējām viņus mūsu valodās sludinām Dieva lielos darbus.
11የቀርጤስና የዓረብ ሰዎች፥ የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን።
12Un visi pārsteigti brīnījās, viens otram sacīdami: Ko tas nozīmē?
12ሁሉም ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው። እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ።
13Bet citi izsmiedami sacīja: Tie ir salda vīna pilni.
13ሌሎች ግን እያፌዙባቸው። ጉሽ የወይን ጠጅ ጠግበዋል አሉ።
14Bet Pēteris, nostājies ar tiem vienpadsmit, paceltā balsī sacīja viņiem: Jūdejas vīri un visi, kas dzīvojat Jeruzalemē, lai tas jums zināms, un savām ausīm uzmaniet manus vārdus:
14ነገር ግን ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ፥ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ሲል ተናገራቸው። አይሁድ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፥ ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ቃሎቼንም አድምጡ።
15Viņi nav iereibuši, kā jūs domājat, jo ir tikai dienas trešā stunda;
15ለእናንተ እንደ መሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም፥ ከቀኑ ሦስተኛ ሰዓት ነውና፤
16Bet tas ir, ko pravietis Joēls sacīja:
16ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል የተባለው ነው።
17Tas būs pēdējās dienās, saka Kungs, es izliešu no sava Gara pār ikvienu miesu, un jūsu dēli un jūsu meitas pravietos, un jūsu jaunieši redzēs parādības, un jūsu sirmgalvji sapņos sapņus.
17እግዚአብሔር ይላል። በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፤
18Un arī pār saviem kalpiem un savām kalponēm es tanīs dienās izliešu no sava Gara, un viņi pravietos.
18ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ።
19Un es došu brīnumzīmes augšā pie debesīm un apakšā virs zemes: asinis un uguni, un dūmu kvēpus;
19ድንቆችን በላይ በሰማይ፥ ምልክቶችንም በታች በምድር እሰጣለሁ፤ ደምም እሳትም የጢስ ጭጋግም ይሆናል፤
20Saule pārvērtīsies tumsā un mēness asinīs, iekams nāks Kunga lielā un redzamā diena.
20ታላቅ የሆነ የተሰማም የጌታ ቀን ሳይመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣሉ።
21Un notiks, ka ikviens, kas Kunga vārdu piesauks, kļūs pestīts. (Jl.2,28-31)
21የጌታን ስም የሚጠራም ሁሉ ይድናል።
22Izraēliešu vīri! Uzklausiet šos vārdus: Jēzu no Nācaretes, šo Vīru, ko Dievs jums apliecinājis spēkā un brīnumos, un zīmēs, ko Dievs caur Viņu darījis jūsu vidū, kā arī jūs to zināt,
22የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤
23To jūs pēc Dieva noteiktā lēmuma un paredzes nodevāt un ar noziedznieku rokām piekalāt krustā, un nonāvējāt.
23እርሱንም በእግዚአብሔር በተወሰነው አሳቡና በቀደመው እውቀቱ ተሰጥቶ በዓመፀኞች እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት።
24Dievs Viņu, atbrīvodams no miroņu valsts ciešanām, uzmodināja, jo tai bija neiespējami Viņu paturēt.
24እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና።
25Jo Dāvids par Viņu saka: Es vienmēr redzēju Kungu savu acu priekšā, jo Viņš ir man pa labi, lai es nešaubītos.
25ዳዊት ስለ እርሱ እንዲህ ይላልና። ጌታን ሁልጊዜ በፊቴ አየሁት፥ እንዳልታወክ በቀኜ ነውና።
26Tāpēc mana sirds priecājās, un mana mēle gavilēja, un arī mana miesa dusēs cerībā.
26ስለዚህ ልቤን ደስ አለው፥ ልሳኔም ሐሤት አደረገ፥ ደግሞም ሥጋዬ በተስፋ ያድራል፤
27Jo Tu neatstāsi manu dvēseli mirušo valstī, nedz dosi savam Svētajam redzēt satrūdēšanu.
27ነፍሴን በሲኦል አትተዋትምና፥ ቅዱስህንም መበስበስን ያይ ዘንድ አትሰጠውም።
28Tu man esi zināmus darījis dzīves ceļus, un ar līksmību Tu mani piepildīsi sava vaiga priekšā.
28የሕይወትን መንገድ አስታወቅኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን ትሞላብኛለህ።
29Brāļi, es uzdrošinos ar jums vaļsirdīgi runāt par patriarhu Dāvidu, ka viņš ir nomiris un aprakts, un viņa kaps pie mums ir līdz šai dienai.
29ወንድሞች ሆይ፥ ስለ አባቶች አለቃ ስለ ዳዊት እንደ ሞተም እንደ ተቀበረም ለእናንተ በግልጥ እናገር ዘንድ ፍቀዱልኝ፤ መቃብሩም እስከ ዛሬ በእኛ ዘንድ ነው።
30Viņš bija pravietis un zināja, ka Dievs viņam zvērēdams apsolīja sēdināt viņa tronī vienu no tā miesas atvasēm. (Ps.131,11)
30ነቢይ ስለ ሆነ፥ ከወገቡም ፍሬ በዙፋኑ ያስቀምጥ ዘንድ እግዚአብሔር መሐላ እንደ ማለለት ስለ አወቀ፥
31Viņš, to paredzēdams, sacīja par Kristus augšāmcelšanos, jo Viņš netika atstāts mirušo valstī, nedz Viņa miesa redzēja satrūdēšanu. (Ps.15,10)
31ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ አስቀድሞ አይቶ፥ ነፍሱ በሲኦል እንዳልቀረች ሥጋውም መበስበስን እንዳላየ ተናገረ።
32Šo Jēzu Dievs cēla augšām, tam mēs visi esam liecinieki.
32ይህን ኢየሱስን እግዚአብሔር አስነሣው ለዚህም ነገር እኛ ሁላችን ምስክሮች ነን፤
33Dieva labās rokas paaugstināts un no Tēva saņēmis Svētā Gara apsolījumu, Viņš izlēja to, ko jūs redzat un dzirdat.
33ስለዚህ በእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ ብሎና የመንፈስ ቅዱስን የተስፋ ቃል ከአብ ተቀብሎ ይህን እናንተ አሁን የምታዩትንና የምትሰሙትን አፈሰሰው።
34Jo Dāvids neuzgāja debesīs, bet pats sacīja: Kungs sacīja manam Kungam: sēdies pie manas labās rokas,
34ዳዊት ወደ ሰማያት አልወጣምና፥ ነገር ግን እርሱ። ጌታ ጌታዬን። ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው
35Iekams es Tavus ienaidniekus lieku par paklāju Tavām kājām. (Ps.109,1)
36አለ። እንግዲህ ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን ኢየሱስን እግዚአብሔር ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ።
36Tāpēc lai viss Izraēļa nams visnoteiktāk zina, ka Dievs padarīja Viņu par Kungu un Kristu, šo Jēzu, ko jūs sitāt krustā.
37ይህንም በሰሙ ጊዜ ልባቸው ተነካ፥ ጴጥሮስንና ሌሎችንም ሐዋርያት። ወንድሞች ሆይ፥ ምን እናድርግ? አሉአቸው።
37Bet viņi, to dzirdot, satriektu sirdi, sacīja Pēterim un pārējiem apustuļiem: Brāļi, ko mums darīt?
38ጴጥሮስም። ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።
38Un Pēteris viņiem sacīja: Gandariet par saviem grēkiem, un ikviens no jums lai kristās Jēzus Kristus vārdā jūsu grēku piedošanai, un jūs saņemsiet Svētā Gara dāvanu.
39የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ ጌታ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነውና አላቸው።
39Jo solījums pieder jums un jūsu bērniem, un visiem, kas tālu ir, kurus Kungs, mūsu Dievs, vēl aicinās.
40በብዙ ሌላ ቃልም መሰከረና። ከዚህ ጠማማ ትውልድ ዳኑ ብሎ መከራቸው።
40Vēl daudz citos vārdos viņš apliecināja un mācīja tos, sacīdams: Glābieties no šīs samaitātās cilts!
41ቃሉንም የተቀበሉ ተጠመቁ፥ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ፤
41Kas viņa vārdus pieņēma, tie kristījās; un tanī dienā pievienojās ap trīs tūkstoši dvēseļu.
42በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።
42Un viņi pastāvēja apustuļu mācībā, maizes laušanas sadraudzībā un lūgšanā.
43ነገር ግን በሰው ሁሉ ፍርሀት ሆነ፤ በሐዋርያትም እጅ ብዙ ድንቅና ምልክት ተደረገ።
43Un ikvienai dvēselei bija bailes, jo apustuļi Jeruzalemē darīja daudzus brīnumus un zīmes, un lielas bailes pārņēma visus.
44ያመኑትም ሁሉ አብረው ነበሩ፤
44Bet visi, kas ticēja, turējās kopā, un viss viņiem bija kopīgs.
45ያላቸውንም ሁሉ አንድነት አደረጉ። መሬታቸውንና ጥሪታቸውንም እየሸጡ፥ ማንኛውም እንደሚፈልግ ለሁሉ ያካፍሉት ነበር።
45Viņi pārdeva savus īpašumus un mantu un izdalīja visiem, kā kuram vajadzēja.
46በየቀኑም በአንድ ልብ ሆነው በመቅደስ እየተጉ በቤታቸውም እንጀራ እየቈረሱ፥ በደስታና በጥሩ ልብ ምግባቸውን ይመገቡ ነበር፤
46Viņi ik dienas vienprātīgi sanāca svētnīcā un mājās lauza maizi, un gavilējot ar vientiesīgu sirdi pieņēma barību,
47እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።
47Godinādami Dievu un iegūdami žēlastību visā tautā. Bet Kungs ik dienas pievienoja viņiem tos, kam vajadzēja kļūt pestītiem.