Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Acts

3

1Pēteris un Jānis gāja svētnīcā ap devīto lūgšanas stundu.
1ጴጥሮስና ዮሐንስም በጸሎት ጊዜ በዘጠኝ ሰዓት ወደ መቅደስ ይወጡ ነበር።
2Tad atnesa kādu vīru, kas bija tizls no mātes miesām. Viņu ik dienas nolika pie tā sauktajām greznajām durvīm, lai viņš lūgtu dāvanas no tiem, kas ieiet svētnīcā.
2ወደ መቅደስም ከሚገቡት ምጽዋት ይለምን ዘንድ፥ ሰዎች ተሸክመው መልካም በሚሉአት በመቅደስ ደጅ በየቀኑ ያስቀምጡት የነበሩ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ አንካሳ የሆነ አንድ ሰው ነበረ።
3Viņš, redzēdams Pēteri un Jāni pirms ieiešanas dievnamā, lūdza no tiem kādu dāvanu.
3እርሱም ጴጥሮስና ዮሐንስ ወደ መቅደስ ሊገቡ እንዳላቸው ባየ ጊዜ፥ ምጽዋትን ለመናቸው።
4Bet Pēteris ar Jāni, uzlūkodami viņu, sacīja: Paskaties uz mums!
4ጴጥሮስም ከዮሐንስ ጋር ትኵር ብሎ ወደ እርሱ ተመልክቶ። ወደ እኛ ተመልከት አለው።
5Un viņš uzlūkoja tos, cerēdams kaut ko no viņiem saņemt.
5እርሱም አንድ ነገር ከእነርሱ እንዲቀበል ሲጠብቅ ወደ እነርሱ ተመለከተ።
6Bet Pēteris sacīja: Sudraba un zelta man nav; bet kas man ir, to es tev dodu: Nācarieša Jēzus Kristus vārdā celies un staigā!
6ጴጥሮስ ግን። ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።
7Un viņš, paņēmis aiz labās rokas, to piecēla; un tūdaļ tā kājas un pēdas nostiprinājās
7በቀኝ እጁም ይዞ አስነሣው፤ በዚያን ጊዜም እግሩና ቍርጭምጭምቱ ጸና፥
8Un tas uzlēcis nostājās un sāka iet, un kopā ar viņiem iegāja svētnīcā, un lēkāja, un godināja Dievu.
8ወደ ላይ ዘሎም ቆመ፥ ይመላለስም ጀመር፤ እየተመላለሰም እየዘለለም እግዚአብሔርንም እያመሰገነ ከእነርሱ ጋር ወደ መቅደስ ገባ።
9Un visa tauta redzēja viņu staigājam un Dievu godinām.
9ሕዝቡም ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገነ ሲመላለስ አዩት፤
10Un viņi pazina to, ka viņš bija tas, kas, dāvanas lūgdams, sēdēja pie greznajām svētnīcas durvīm; un tos pārņēma izbrīns un bailes par to, kas viņam bija noticis.
10መልካምም በሚሉአት በመቅደስ ደጅ ስለ ምጽዋት ተቀምጦ የነበረው እርሱ እንደ ሆነ አወቁት፤ በእርሱም ከሆነው የተነሣ መደነቅና መገረም ሞላባቸው።
11Bet kad viņš turējās kopā ar Pēteri un Jāni, tad visa tauta brīnīdamās saskrēja ap viņiem tā sauktajā Salomona priekštelpā.
11እርሱም ጴጥሮስንና ዮሐንስን ይዞ ሳለ፥ ሕዝቡ ሁሉ እየተደነቁ የሰሎሞን ደጅ መመላለሻ በሚባለው አብረው ወደ እነርሱ ሮጡ።
12To redzēdams, Pēteris sacīja tautai: Izraēliešu vīri, ko jūs brīnāties par to, vai ko skatāties uz mums it kā mēs ar savu spēku un varu būtu padarījuši to, ka šis staigā?
12ጴጥሮስም አይቶ ለሕዝቡ እንዲህ ሲል መለሰ። የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ በዚህ ስለ ምን ትደነቃላችሁ? ወይስ በገዛ ኃይላችን ወይስ እግዚአብሔርን በመፍራታችን ይህ ይመላለስ ዘንድ እንዳደረግነው ስለ ምን ትኵር ብላችሁ ታዩናላችሁ?
13Ābrahama Dievs un Īzāka Dievs, un Jēkaba Dievs, mūsu tēvu Dievs pagodināja savu Dēlu Jēzu, ko jūs nodevāt un noliedzāt Pilāta priekšā, kad tas nolēma Viņu atbrīvot.
13የአብርሀምና የይስሐቅ የያዕቆብም አምላክ፥ የአባቶቻችን አምላክ፥ እናንተ አሳልፋችሁ የሰጣችሁትንና ሊፈታው ቈርጦ ሳለ በጲላጦስ ፊት የካዳችሁትን ብላቴናውን ኢየሱስን አከበረው።
14Svēto un Taisnīgo jūs noliedzāt un lūdzāt, lai jums dod slepkavu.
14እናንተ ግን ቅዱሱን ጻድቁንም ክዳችሁ ነፍሰ ገዳዩን ሰው ይሰጣችሁ ዘንድ ለመናችሁ፥
15Un dzīvības devēju jūs nonāvējāt, bet Dievs Viņu uzmodināja no miroņiem. Tam mēs esam liecinieki.
15የሕይወትንም ራስ ገደላችሁት፤ እርሱን ግን እግዚአብሔር ከሙታን አስነሣው፥ ለዚህም ነገር እኛ ምስክሮች ነን።
16Un ticības dēļ Viņa vārdam šo, kuru jūs redzat un pazīstat, Viņa vārds stiprināja; un ticība, kas no Viņa ir, dāvāja tam pilnīgu veselību visu jūsu priekšā.
16በስሙም በማመን ይህን የምታዩትንና የምታውቁትን የእርሱ ስም አጸናው፥ በእርሱም በኩል የሆነው እምነት በሁላችሁ ፊት ይህን ፍጹም ጤና ሰጠው።
17Bet tagad brāļi, es zinu, ka jūs tāpat kā jūsu priekšnieki nezināšanas dēļ to padarījāt.
17አሁንም፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ እንደ አለቆቻችሁ ደግሞ ባለማወቅ እንዳደረጋችሁት አውቄአለሁ፤
18Jo Dievs to tā izpildīja, kā ar visu praviešu mutēm priekšsludinājis, ka Kristum jācieš.
18እግዚአብሔር ግን ክርስቶስ መከራ እንዲቀበል አስቀድሞ በነቢያት ሁሉ አፍ የተናገረውን እንዲሁ ፈጸመው።
19Tāpēc nožēlojiet grēkus un atgriezieties, lai jūsu grēki tiktu izdeldēti!
19እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም።
20Un lai Kungs dotu atspirgšanas laikus, lai sūtītu To, ko Viņš jums priekšsludinājis, Jēzu Kristu.
21እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተናገረው፥ ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።
21Ko debesīm vajag uzņemt līdz tam laikam, kad viss būs piepildīts, ko Dievs runājis no mūžības ar savu svēto praviešu muti.
22ሙሴም ለአባቶች። ጌታ አምላክ እኔን እንዳስነሣኝ ነቢይን ከወንድሞቻችሁ ያስነሣላችኋል፤ በሚነግራችሁ ሁሉ እርሱን ስሙት።
22Jo Mozus sacīja: Kungs, jūsu Dievs, iecels jums pravieti no jūsu brāļiem tāpat kā mani; Viņu jūs klausīsiet visās lietās, ko vien Viņš jums runās. (5.Moz.18,15)
23ያንም ነቢይ የማትሰማው ነፍስ ሁሉ ከሕዝብ ተለይታ ትጠፋለች አለ።
23Un notiks, ka ikviena dvēsele, kas šo pravieti neklausīs, tiks no tautas vidus izskausta. (5.Moz.18,19)
24ሁለተኛም ከሳሙኤል ጀምሮ ከእርሱም በኋላ የተናገሩት ነቢያት ሁሉ ደግሞ ስለዚህ ወራት ተናገሩ።
24Un visi pravieši, kas runājuši, sākot ar Samuēlu un turpmāk, pasludināja šīs dienas.
25እናንተ የነቢያት ልጆችና እግዚአብሔር ለአብርሃም። በዘርህ የምድር ወገኖች ሁሉ ይባረካሉ ብሎ፥ ከአባቶቻችን ጋር ያደረገው የኪዳን ልጆች ናችሁ።
25Jūs esat praviešu un derības, ko Dievs slēdzis ar mūsu tēviem, bērni, jo Viņš sacīja Ābrahamam: Un tavos pēcnācējos tiks svētītas visas zemes ciltis.
26ለእናንተ አስቀድሞ እግዚአብሔር ብላቴናውን አስነሥቶ፥ እያንዳንዳችሁን ከክፋታችሁ እየመለሰ ይባርካችሁ ዘንድ፥ ሰደደው።
26Dievs dodams savu Dēlu, vispirms sūtīja Viņu pie jums, lai Viņš jūs svētītu, lai ikviens atgrieztos no saviem ļaunajiem darbiem.