Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Acts

21

1Bet notika, ka mēs no viņiem šķīrāmies. Taisnā ceļā braukdami, nonācām Kosā un nākošajā dienā Rodā, un no turienes Patrā;
1ከእነርሱም ተለይተን ተነሣን፤ በቀጥታም ሄደን ወደ ቆስ በነገውም ወደ ሩድ ከዚያም ወደ ጳጥራ መጣን፤
2Un mēs, atraduši kuģi, kas brauc uz Feniķiju, iekāpām un aizbraucām.
2ወደ ፊንቄም የሚሻገር መርከብ አግኝተን ገባንና ተነሣን።
3Bet kad ieraudzījām Kipru un atstājām to pa kreisi, braucām uz Sīriju un nonācām Tirā, jo tur kuģim bija jāizkrauj krava.
3ቆጵሮስንም ባየናት ጊዜ በስተ ግራችን ተውናት ወደ ሶርያም ሄደን ወደ ጢሮስ ደረስን፥ መርከቡ ሸክሙን በዚያ የሚያራግፍ ነበርና።
4Atraduši mācekļus, mēs tur palikām septiņas dienas. Tie, Gara pamudināti, sacīja Pāvilam, lai viņš neiet uz Jeruzalemi.
4ደቀ መዛሙርትንም ባገኘን ጊዜ በዚያ ሰባት ቀን ተቀመጥን፤ እነርሱም ጳውሎስን ወደ ኢየሩሳሌም እንዳይወጣ በመንፈስ አሉት።
5Kad šīs dienas bija pagājušas, mēs kājām devāmies ceļā. Visi kopā ar sievām un bērniem mūs pavadīja vēl ārpus pilsētas; un mēs jūrmalā, ceļos nometušies, lūdzām Dievu.
5ጊዜውንም በፈጸምን ጊዜ ወጥተን ሄድን፤ ሁላቸውም ከሚስቶቻቸውና ከልጆቻቸው ጋር እስከ ከተማው ውጭ ድረስ ሸኙን፥ በባሕሩም ዳር ተንበርክከን ጸለይን፤
6Atvadījušies savā starpā, mēs iekāpām kuģī, bet viņi aizgāja savās mājās.
6እርስ በርሳችንም ተሰነባብተን ወደ መርከብ ወጣን፥ እነዚያም ወደ ቤታቸው ተመለሱ።
7No Tiras nonākuši Ptolemaidā, mēs pabeidzām jūras braucienu un, apsveikuši brāļus, palikām pie viņiem vienu dienu.
7እኛም የባሕሩን መንገድ ጨርሰን ከጢሮስ ወደ አካ ደረስን፥ ለወንድሞችም ሰላምታ ሰጥተን ከእነርሱ ዘንድ አንድ ቀን ተቀመጥን።
8Bet nākošajā dienā mēs devāmies ceļā un nonācām Cēzarejā. Iegājuši evaņģēlista Filipa, kas bija viens no septiņiem, namā, mēs palikām pie viņa.
8በነገውም ወጥተን ወደ ቂሣርያ መጣን፥ ከሰባቱም አንድ በሚሆን በወንጌላዊው ፊልጶስ ቤት ገብተን በእርሱ ዘንድ ተቀመጥን።
9Viņam bija četras meitas, jaunavas, kuras pravietoja.
9ለእርሱም ትንቢት የሚናገሩ አራት ደናግል ሴቶች ልጆች ነበሩት።
10Un kad mēs tur dažas dienas uzkavējāmies, no Jūdejas atnāca kāds pravietis, vārdā Agabs.
10አያሌ ቀንም ተቀምጠን ሳለን ነቢይ የነበረ አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ከይሁዳ ወረደ።
11Tas, ieradies pie mums, paņēma Pāvila jostu un, saistījis sev kājas un rokas, sacīja: To saka Svētais Gars: tā jūdi Jeruzalemē saistīs vīru, kam šī josta pieder, un nodos pagānu rokās.
11ወደ እኛም መጣና የጳውሎስን መታጠቂያ ወስዶ የገዛ እጁንና እግሩን አስሮ። እንዲሁ መንፈስ ቅዱስ። ይህ መታጠቂያ ያለውን ሰው አይሁድ በኢየሩሳሌም እንደዚህ ያስሩታል በአሕዛብም እጅ አሳልፈው ይሰጡታል ይላል አለ።
12To dzirdēdami, mēs un tie, kas tanī vietā bija, lūdzām, lai viņš neiet uz Jeruzalemi.
12ይህንም በሰማን ጊዜ እኛም በዚያ የሚኖሩትም ወደ ኢየሩሳሌም እንዳይወጣ ለመንነው።
13Tad Pāvils atbildēja un sacīja: Ko jūs darāt, kāpēc raudat un skumdināt manu sirdi? Kunga Jēzus vārda dēļ es esmu sagatavojies, lai mani Jeruzalemē ne tikai sasietu, bet arī mirt.
13ጳውሎስ ግን መልሶ። እያለቀሳችሁ ልቤንም እየሰበራችሁ ምን ማድረጋችሁ ነው? እኔ ስለ ጌታ ስለ ኢየሱስ ስም በኢየሩሳሌም ለመሞት እንኳ ተሰናድቼአለሁ እንጂ ለእስራት ብቻ አይደለም አለ።
14Nespēdami viņu pierunāt, mēs nomierinājāmies, sacīdami: Lai notiek Kunga prāts!
14ምክርንም ሊቀበል እምቢ ባለ ጊዜ። የጌታ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን።
15Pēc šīm dienām mēs sagatavojāmies un gājām uz Jeruzalemi.
15ከዚህም ቀን በኋላ ተዘጋጅተን ወደ ኢየሩሳሌም ወጣን።
16Bet daži mācekļi no Cēzarejas nāca kopā ar mums. Viņi atveda līdz kādu kiprieti Mnasonu, seno mācekli, pie kura mums bija jāņem mājvieta.
16በቂሣርያም ከነበሩ ደቀ መዛሙርት አንዳንዶች ደግሞ ከእኛ ጋር መጡ፥ እነርሱም ወደምናድርበት ወደ ቀደመው ደቀ መዝሙር ወደ ቆጵሮሱ ምናሶን ወደሚሉት ቤት መሩን።
17Kad nonācām Jeruzalemē, brāļi mūs labprāt uzņēma.
17ወደ ኢየሩሳሌም በደረስን ጊዜ ወንድሞች በደስታ ተቀበሉን።
18Nākošajā dienā Pāvils kopā ar mums aizgāja pie Jēkaba, kur sapulcējās visi vecākie.
18በነገውም ጳውሎስ ከእኛ ጋር ወደ ያዕቆብ ዘንድ ገባ ሽማግሌዎችም ሁሉ መጡ።
19Tos apsveicis, viņš pēc kārtas izstāstīja, ko Dievs ar viņa kalpošanu darījis pagāniem.
19ሰላምታም ካቀረበላቸው በኋላ በእርሱ ማገልገል እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ያደረገውን በእያንዳንዱ ተረከላቸው።
20To dzirdējuši, tie godināja Dievu un sacīja viņam: Brāli, tu redzi, cik tūkstoši jūdu ir, kas palikuši ticīgi, un visi tie bauslības piekritēji.
20እነርሱም በሰሙ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑ አሉትም። ወንድም ሆይ፥ በአይሁድ መካከል አምነው የነበሩት ስንት አእላፋት እንደ ሆኑ ታያለህ፤ ሁላቸውም ለሕግ የሚቀኑ ናቸው።
21Bet viņi dzirdēja par tevi, ka tu tos jūdus, kas dzīvo starp pagāniem, mācot atkrist no Mozus, sacīdams, ka tiem nevajagot apgraizīt savus bērnus un dzīvot pēc ieražām.
21ልጆቻቸውንም እንዳይገርዙ በሥርዓትም እንዳይሄዱ ብለህ በአሕዛብ መካከል ያሉት አይሁድ ሁሉ ሙሴን ይክዱ ዘንድ እንድታስተምር ስለ አንተ ነግረዋቸዋል።
22Ko darīt? Katrā ziņā tautai jāsapulcējas, jo dzirdēs, ka tu atnācis.
22እንግዲህ ምን ይሁን? የአንተን መምጣት ይሰማሉና ብዙዎች የግድ ሳይሰበሰቡ አይቀሩም።
23Tāpēc dari to, ko mēs tev sakām. Mums ir četri vīri, kas devuši solījumus.
23እንግዲህ ይህን የምንልህን አድርግ፤ ስለት ያለባቸው አራት ሰዎች በእኛ ዘንድ አሉ።
24Ņem tos pie sevis, šķīsties kopā ar viņiem un samaksā par tiem, lai viņi apcērp galvas, tad visi zinās, ka tas, ko par tevi dzirdējuši, ir netaisnība, bet ka arī tu pats dzīvo pēc bauslības.
24እነዚህንም ይዘህ ከእነርሱ ጋር ንጻ፥ ራሳቸውንም እንዲላጩ ገንዘብ ክፈልላቸው፤ ሁሉም ስለ አንተ የተማሩት ከንቱ እንደ ሆነና አንተ ራስህ ደግሞ ሕጉን እየጠበቅህ በሥርዓት እንድትመላለስ ያውቃሉ።
25Bet par tiem, kas no pagāniem kļuvuši ticīgi, mēs nolēmām un rakstījām, lai viņi sargās no tā, kas elkiem upurēts, un asinīm, un nožņaugtā, un netiklības.
25አምነው ስለ ነበሩ አሕዛብ ግን ለጣዖት ከተሠዋ ከደምም ከታነቀም ከዝሙትም ነፍሳቸውን እንዲጠብቁ ፈርደን እኛ ጽፈንላቸዋል።
26Tad Pāvils, paņēmis vīrus pie sevis, nākošajā dienā kopā ar tiem šķīstījās, iegāja svētnīcā, pasludinādams šķīstīšanās dienu izbeigšanos, tiklīdz par ikvienu no tiem būšot upurēts upuris.
26በዚያን ጊዜ ጳውሎስ ሰዎችን ይዞ በማግሥቱ ከእነርሱ ጋር እየነጻ፥ መንጻታቸውን የሚፈጽሙበትን ቀን አስታውቆ ወደ መቅደስ ገባ። በዚያም ቀን ስለ እያንዳንዳቸው መሥዋዕትን አቀረቡ።
27Bet kamēr pagāja septiņas dienas, tie jūdi, kas bija no Āzijas, redzēdami viņu svētnīcā, sakūdīja visu tautu un, sagrābuši viņu, kliedza:
27ሰባቱ ቀንም ይፈጸም ዘንድ ሲቀርብ ከእስያ የመጡ አይሁድ በመቅደስ አይተውት ሕዝብን ሁሉ አወኩና። የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ እርዱን ሕዝብን ሕግንም ይህንም ስፍራ ሲቃወም ሰውን ሁሉ በየስፍራው የሚያስተምረው ሰው ይህ ነው፤ ጨምሮም የግሪክን ሰዎች ደግሞ ወደ መቅደስ አግብቶ ይህን የተቀደሰ ስፍራ አርክሶአል ብለው እየጮኹ እጃቸውን ጫኑበት።
28Izraēliešu vīri, palīdziet! Šis ir tas cilvēks, kas visur visus māca pret tautu, bauslību un šo vietu; turklāt arī pagānus viņš ievedis svētnīcā un tā apgānījis šo svēto vietu;
29በፊት የኤፌሶኑን ጥሮፊሞስን ከእርሱ ጋር በከተማ አይተውት ነበርና ጳውሎስም ወደ መቅደስ ያገባው መስሎአቸው ነው።
29Jo tie redzēja efezieti Trofimu pilsētā kopā ar viņu un domāja, ka Pāvils to ievedis svētnīcā.
30ከተማውም ሁሉ ታወከ ሕዝቡም ሁሉ ተሰበሰቡ ጳውሎስንም ይዘው ከመቅደስ ውጭ ጎተቱት፥ ወዲያውም ደጆች ተዘጉ።
30Tad visa pilsēta uztraucās, ļaudis saskrēja un, satvēruši Pāvilu, vilka to no svētnīcas ārā; un tūdaļ durvis aizslēdza.
31ሊገድሉትም ሲፈልጉ። ኢየሩሳሌም ፈጽማ ታወከች የሚል ወሬ ወደ ጭፍራው ሻለቃ ወጣ፤
31Kad tie gribēja viņu nonāvēt, tika paziņots sardzes priekšniekam, ka visā Jeruzalemē ir sacelšanās.
32እርሱም ያን ጊዜ ወታደሮችን ከመቶ አለቆች ጋር ይዞ እየሮጠ ወረደባቸው፤ እነርሱም የሻለቃውንና ወታደሮችን ባዩ ጊዜ ጳውሎስን መምታት ተዉ።
32Paņēmis kareivjus un virsniekus, viņš tūdaļ aizskrēja pie tiem. Tie, redzēdami priekšnieku un kareivjus, mitējās sist Pāvilu.
33በዚያን ጊዜም የሻለቃው ቀርቦ ያዘውና በሁለት ሰንሰለት ይታሰር ዘንድ አዞ ማን እንደ ሆነና ምን እንዳደረገ ጠየቀ።
33Tad priekšnieks piegāja, satvēra viņu, pavēlēja sasiet to divām važām un vaicāja, kas viņš tāds un ko viņš darījis?
34ሕዝቡም እኵሌቶቹ እንዲህ እኵሌቶቹም እንዲያ እያሉ ይጮኹ ነበር፤ ስለ ጫጫታውም እርግጡን ማወቅ ባልተቻለ ጊዜ፥ ወደ ወታደሮች ሰፈር ይወስዱት ዘንድ አዘዘ።
34Bet pūlī daži kliedza šo, citi to. Nevarēdams troksnī nekā noteikta uzzināt, viņš pavēlēja aizvest to uz kareivju mītni.
35ወደ ደረጃውም በደረሰ ጊዜ ስለ ሕዝቡ ግፊያ ወታደሮች እንዲሸከሙት ሆነ፤
35Kad viņš nonāca līdz kāpnēm, notika, ka kareivji viņu nesa ļaužu uzmākšanās dēļ;
36ብዙ ሕዝብ። አስወግደው እያሉና እየጮኹ ይከተሉ ነበርና።
36Jo daudz ļaužu sekoja, kliegdami: Nost ar viņu!
37ወደ ሰፈርም ሊያገቡት በቀረቡ ጊዜ፥ ጳውሎስ የሻለቃውን። አንድ ነገር ብነግርህ ትፈቅዳለህን? አለው። እርሱም። የግሪክ ቋንቋ ታውቃለህን?
37Pirms Pāvilu ieveda kareivju mītnē, viņš sacīja priekšniekam: Vai man atļauts tev ko teikt? Tas sacīja: Vai tu grieķiski proti?
38አንተ ከዚህ ዘመን አስቀድሞ ከነፍሰ ገዳዮቹ አራቱን ሺህ ሰዎች አሸፍተህ ወደ ምድረ በዳ ያወጣህ የግብፅ ሰው አይደለህምን? አለ።
38Vai tu neesi tas ēģiptietis, kas pirms dažām dienām sacēla dumpi un aizveda tuksnesī četrus tūkstošus sikariešu vīru?
39ጳውሎስ ግን። እኔስ አይሁዳዊ በኪልቅያ ያለው የጠርሴስ ሰው ሆኜ ስመ ጥር በሆነ ከተማ የምኖር ነኝ፤ ለሕዝቡ እናገር ዘንድ እንድትፈቅድልኝ እለምንሃለሁ አለ።
39Un Pāvils sacīja viņam: Es esmu jūdu cilvēks, tarsietis, ievērojamās Kilikijas pilsētas pilsonis; es tevi lūdzu, atļauj man runāt tautai.
40በፈቀደለትም ጊዜ ጳውሎስ በደረጃው ላይ ቆሞ በእጁ ወደ ሕዝቡ ጠቀሰ እጅግም ጸጥታ በሆነ ጊዜ በዕብራይስጥ ቋንቋ እየተናገረ እንዲህ አለ።
40Kad viņš to atļava, Pāvils, uz kāpnēm stāvēdams, māja ļaudīm ar roku un dziļam klusumam iestājoties, runāja ebreju valodā, sacīdams: