Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Acts

22

1Brāļi un tēvi, uzklausiet tagad aizstāvēšanos, kādu es jums teikšu!
1እናንተ ወንድሞች አባቶችም፥ አሁን ለእናንተ ነገሬን ስገልጥ ስሙኝ።
2Kad tie dzirdēja, ka viņš tos uzrunā ebreju valodā, tie kļuva vēl klusāki,
2በዕብራይስጥም ቋንቋ ሲናገር በሰሙ ጊዜ ከፊት ይልቅ ዝም አሉ። እርሱም አለ።
3Un viņš sacīja: Es esmu jūds, dzimis Tarsā, Kilikijā, bet uzaudzināts šinī pilsētā, izglītojies pie Gamaliēla kājām saskaņā ar tēvu bauslības patiesībām, bauslības cīnītājs, kādi arī jūs šodien visi esat;
3እኔ የኪልቅያ በምትሆን በጠርሴስ የተወለድሁ፥ በዚችም ከተማ በገማልያል እግር አጠገብ ያደግሁ፥ የአባቶችንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፥ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ሰው ነኝ
4Un šo mācību esmu vajājis līdz nāvei, saistīdams un nododams cietumā vīriešus un sievietes,
4ወንዶችንም ሴቶችንም እያሰርሁ ወደ ወኅኒም አሳልፌ እየሰጠሁ ይህን መንገድ እስከ ሞት ድረስ አሳደድሁ።
5Kā to man apliecina augstais priesteris un visi vecākie, no kuriem, saņēmis vēstules, gāju pie brāļiem uz Damasku, lai no turienes tos sasaistītus vestu uz Jeruzalemi un sodītu.
5እንዲህም ሊቀ ካህናቱ ደግሞ ሽማግሌዎቹም ሁሉ ይመሰክሩልኛል፤ ከእነርሱ ደግሞ መልእክትን ለወንድሞቻቸው ተቀብዬ፥ በደማስቆ ያሉትን ደግሞ ታስረው እንዲቀጡ ወደ ኢየሩሳሌም ላመጣ ወደዚያ እሄድ ነበር።
6Bet notika, ka, man ejot un dienas vidū tuvojoties Damaskai, piepeši mani apspīdēja spilgta gaisma no debesīm.
6ስሄድም ወደ ደማስቆ በቀረብሁ ጊዜ፥ ቀትር ሲሆን ድንገት ከሰማይ ታላቅ ብርሃን በዙሪያዬ አንጸባረቀ፤
7Un es nokritu zemē un dzirdēju balsi man sakām: Saul, Saul, kāpēc tu mani vajā?
7በምድርም ላይ ወድቄ። ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለኝን ድምፅ ሰማሁ።
8Bet es atbildēju: Kungs, kas tu esi? Un Viņš sacīja man: Es esmu Jēzus Nācarietis, ko tu vajā.
8እኔም መልሼ። ጌታ ሆይ፥ አንተ ማን ነህ? አልሁ። እርሱም። አንተ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ እኔ ነኝ አለኝ።
9Un tie, kas bija kopā ar mani, gaismu gan redzēja, bet Viņa balsi, kas ar mani runāja, nedzirdēja.
9ከእኔ ጋር የነበሩትም ብርሃኑን አይተው ፈሩ፥ የሚናገረኝን የእርሱን ድምፅ ግን አልሰሙም።
10Es sacīju: Kungs, kas man jādara? Bet Kungs sacīja man: Celies, ej uz Damasku, un tur tev pateiks visu, kas tev jādara.
10ጌታ ሆይ፥ ምን ላድርግ? አልሁት። ጌታም። ተነሥተህ ወደ ደማስቆ ሂድና ታደርገው ዘንድ ስለ ታዘዘው ሁሉን በዚያ ይነግሩሃል አለኝ።
11Un tā kā es no tās gaismas spilgtuma nevarēju vairs redzēt, pavadoņi veda mani aiz rokas, un tā es nonācu Damaskā.
11ከዚያ ብርሃንም ክብር የተነሣ ማየት ባይሆንልኝ ከእኔ ጋር የነበሩት ሰዎች እጄን ይዘው እየመሩኝ ወደ ደማስቆ ደረስሁ።
12Tur Ananija, bauslības vīrs, par ko liecina visi tur dzīvojošie jūdi,
12በዚያም የኖሩት አይሁድ ሁሉ የመሰከሩለት እንደ ሕጉም በጸሎት የተጋ ሐናንያ የሚሉት አንድ ሰው ነበረ።
13Atnāca un, nostājies pie manis, sacīja man: Brāli Saul, topi redzīgs! Un es tanī pat stundā uzlūkoju viņu,
13እርሱም ወደ እኔ መጥቶ በአጠገቤም ቆሞ። ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ እይ አለኝ። እኔም ያን ጊዜውን ወደ እርሱ አየሁ።
14Bet viņš sacīja: Mūsu tēvu Dievs tevi izredzējis, lai tu atzītu Viņa prātu un redzētu Taisnīgo, un dzirdētu balsi no Viņa mutes;
14እርሱም አለኝ። የአባቶቻችን አምላክ ፈቃዱን ታውቅ ዘንድና ጻድቁን ታይ ዘንድ ከአፉም ድምፅን ትሰማ ዘንድ አስቀድሞ መርጦሃል
15Jo tu visiem ļaudīm liecināsi par Viņu to, ko redzēji un dzirdēji.
15ባየኸውና በሰማኸው በሰው ሁሉ ፊት ምስክር ትሆንለታለህና።
16Un ko tagad vēl kavējies? Celies un pieņem kristību, un, Viņa vārdu piesaucis, nomazgā savus grēkus!
16አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።
17Bet notika, kad atgriezos Jeruzalemē un svētnīcā lūdzu Dievu, ka es tiku garā aizrauts;
17ወደ ኢየሩሳሌምም ከተመለሱ በኋላ በመቅደስ ስጸልይ ተመስጦ መጣብኝ፥
18Un es redzēju Viņu man sakām: Steidzies un žigli izej no Jeruzalemes, jo viņi tavu liecību par mani nepieņems.
18እርሱም። ፍጠን ከኢየሩሳሌምም ቶሎ ውጣ፥ ስለ እኔ የምትመሰክረውን አይቀበሉህምና ሲለኝ አየሁት።
19Un es sacīju: Kungs, viņi zina, ka es tos, kas uz Tevi ticēja, metu cietumā un šaustīju sinagogās.
19እኔም። ጌታ ሆይ፥ በአንተ የሚያምኑትን በምኵራብ ሁሉ እኔ በወኅኒ አገባና እደበድብ እንደ ነበርሁ እነርሱ ያውቃሉ፤
20Un kad Tava liecinieka Stefana asinis tika izlietas, es biju klāt un piekritu tam, un sargāju drēbes tiem, kas viņu nonāvēja.
20የሰማዕትህንም የእስጢፋኖስን ደም ባፈሰሱ ጊዜ፥ ራሴ ደግሞ በአጠገባቸው ስቆም ተስማምቼ የገዳዮችን ልብስ እጠብቅ ነበር አልሁ።
21Un Viņš man sacīja: Ej, jo es tevi sūtīšu tālumā starp pagāniem.
21እርሱም። ሂድ፥ እኔ ወደ አሕዛብ ከዚህ ወደ ሩቅ እልክሃለሁና አለኝ።
22Uzklausījuši viņu līdz šiem vārdiem, tie pacēla savas balsis, sacīdami: Nost tādu no šīs zemes, jo tāds nedrīkst dzīvot!
22እስከዚህም ቃል ድረስ ይሰሙት ነበር፥ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው። እንደዚህ ያለውን ሰው ከምድር አስወግደው፥ በሕይወት ይኖር ዘንድ አይገባውምና አሉ።
23Bet, kad tie kliedza un nometa savas drēbes, un svieda putekļus gaisā,
23ሲጮኹና ልብሳቸውን ሲወረውሩ ትቢያንም ወደ ላይ ሲበትኑ፥
24Priekšnieks lika viņu ievest mītnē, šaustīt rīkstēm un mocīt viņu, lai uzzinātu, kāda iemesla dēļ tie tā kliedza uz viņu.
24የሻለቃው ወደ ሰፈሩ እንዲያገቡት አዘዘ፥ እንደዚህም የጮኹበትን ምክንያት ያውቅ ዘንድ። እየገረፋችሁ መርምሩት አላቸው።
25Un kad tie sasēja viņu siksnām, Pāvils sacīja virsniekam, kas stāvēja viņam klāt: Vai jums atļauts šaustīt nenotiesātu Romas pilsoni?
25በጠፍርም በገተሩት ጊዜ ጳውሎስ በአጠገቡ የቆመውን የመቶ አለቃ። የሮሜን ሰው ያለ ፍርድ ትገርፉ ዘንድ ተፈቅዶላችኋልን? አለው።
26To dzirdējis, virsnieks aizgāja pie priekšnieka un paziņoja viņam, sacīdams: Ko tu gribi darīt? Šis cilvēks taču ir Romas pilsonis.
26የመቶ አለቃውም በሰማ ጊዜ ወደ ሻለቃው ቀርቦ። ይህ ሰው ሮማዊ ነውና ታደርገው ዘንድ ካለህ ተጠበቅ ብሎ ነገረው።
27Tad priekšnieks, piegājis, jautāja viņam: Saki man, vai tu esi romietis? Un viņš sacīja: Jā!
27የሻለቃውም ቀርቦ። አንተ ሮማዊ ነህን? ንገረኝ አለው፤ እርሱም። አዎን አለ።
28Tad priekšnieks atbildēja: Es šo pilsonību ieguvu par augstu maksu. Un Pāvils sacīja: Bet es tāds jau esmu dzimis.
28የሻለቃውም መልሶ። እኔ ይህን ዜግነት በብዙ ገንዘብ አገኘሁት አለ። ጳውሎስም። እኔ ግን በእርስዋ ተወለድሁ አለ።
29Tad tūdaļ aizgāja no viņa tie, kas taisījās viņu mocīt. Bet priekšnieks, uzzinājis, ka viņš ir Romas pilsonis, izbijās, jo bija viņu saistījis.
29ስለዚህም ሊመረምሩት ያሰቡት ከእርሱ ወዲያው ተለዩ፤ የሻለቃውም ደግሞ ሮማዊ መሆኑን ባወቀ ጊዜ ፈራ፥ አሳስሮት ነበርና።
30Bet nākošajā dienā, gribēdams skaidrāk zināt, kāpēc jūdi viņu apsūdz, viņš to atbrīvoja un, pavēlējis sanākt priesteriem un visai augstajai tiesai, izveda Pāvilu un nostādīja viņu starp tiem.
30በማግሥቱም አይሁድ የከሰሱት በምን ምክንያት እንደ ሆነ እርግጡን ያውቅ ዘንድ አስቦ ፈታው፥ የካህናት አለቆችና ሸንጎውም ሁሉ ይሰበሰቡ ዘንድ አዘዘ፥ ጳውሎስንም አውርዶ በፊታቸው አቆመው።