1Bet galvenais tanī, kas pārrunājams, ir tas, ka mums tāds augstais priesteris, kas debesīs nosēdies Majestātes troņa labajā pusē,
1ከተናገርነውም ዋና ነገሩ ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፤
2Būdams svētnīcas un īstās telts kalpotājs. To uzcēlis Kungs, bet ne cilvēks.
2እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፥ እርስዋም በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለች ናት።
3Jo katrs augstais priesteris tiek iecelts dāvanu un upuru nešanai, kāpēc nepieciešami, ka Viņam būtu kaut kas, ko upurēt.
3ሊቀ ካህናት ሁሉ መባንና መሥዋዕትን ሊያቀርብ ይሾማልና፤ ስለዚህም ለዚህ ደግሞ የሚያቀርበው አንዳች ሊኖረው የግድ ነው።
4Ja Viņš būtu virs zemes, Viņš nebūtu priesteris, tāpēc ka šeit ir tādi, kas upurē dāvanas saskaņā ar bauslību,
4እንግዲህ በምድር ቢኖርስ፥ እንደ ሕግ መባን የሚያቀርቡት ስላሉ፥ ካህን እንኳ ባልሆነም፤
5Kas kalpo tā attēlam un ēnai, kas debesīs. Arī Mozum bija norādīts, kad viņš taisīja telti: Lūk, (tā bija teikts) padari visu pēc parauga, kas tev kalnā parādīts!
5እነርሱም ሙሴ ድንኳኒቱን ሊሠራ ሳለ እንደ ተረዳ፥ ለሰማያዊ ነገር ምሳሌና ጥላ የሚሆነውን ያገለግላሉ። በተራራው እንደ ተገለጠልህ ምሳሌ ሁሉን ታደርግ ዘንድ ተጠንቀቅ ብሎት ነበርና።
6Bet tagad Viņam piešķirtā kalpošana labāka tik, par cik labāka derība, kuras starpnieks Viņš ir, jo tā dibināta ar labākiem solījumiem.
6አሁን ግን በሚሻል ተስፋ ቃል በተመሠረተ በሚሻል ኪዳን ደግሞ መካከለኛ እንደሚሆን በዚያ ልክ እጅግ የሚሻል አገልግሎት አግኝቶአል።
7Jo ja pirmā būtu bijusi bez vainas, tad nemeklētu vietu otrai.
7ፊተኛው ኪዳን ነቀፋ ባይኖረው፥ ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር።
8Un tos peldams, Viņš saka: Lūk, nāk dienas, saka Kungs, un es nodibināšu jaunu derību ar Izraēļa namu un ar Jūdas namu.
8እነርሱን እየነቀፈ ይላቸዋልና። እነሆ፥ ከእስራኤል ቤትና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ኪዳን የምገባበት ወራት ይመጣል ይላል ጌታ፤
9Ne tādu derību, kādu nodibināju ar viņu tēviem tanī dienā, kad satvēru viņu roku, lai izvestu tos no Ēģiptes zemes, jo viņi paši nav palikuši manā derībā, un es viņus atmetu, saka Kungs.
9ከግብፅ አገር አወጣቸው ዘንድ እጃቸውን በያዝሁበት ቀን ከአባቶቻቸው ጋር እንደገባሁት ኪዳን አይደለም፤ እነርሱ በኪዳኔ አልጸኑምና፥ እኔም ቸል አልኋቸው ይላል ጌታ።
10Bet šī ir derība, ko es nodibināšu ar Izraēļa namu pēc šīm dienām, saka Kungs: Es likšu savus likumus viņu prātā un ierakstīšu tos viņu sirdīs, un es būšu viņiem Dievs, un viņi būs mana tauta.
10ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፥ እኔም አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑልኛል።
11Un neviens nemācīs savu tuvāko un neviens savu brāli sacīdams: Pazīsti Kungu, jo visi viņi no mazākā līdz lielākajam pazīs mani,
11እያንዳንዱም ጐረቤቱን እያንዳንዱም ወንድሙን። ጌታን እወቅ ብሎ አያስተምርም ከታናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ድረስ ሁሉ ያውቁኛልና።
12Jo es būšu žēlīgs viņu netaisnībām un viņu grēkus vairs nepieminēšu.
12ዓመፃቸውን እምራቸዋለሁና፥ ኃጢአታቸውንም ደግሜ አላስብም።
13Ja Viņš runā par jauno, tad novecojusi agrākā: bet kas novecojis un kļūst nespēcīgs, tas tuvu iznīcībai.
13አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል፤ አሮጌና ውራጅ የሆነውስ ሊጠፋ ቀርቦአል።