Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

James

3

1Mani brāļi, daudzi netopiet mācītāji, zinādami, ka jūs nokļūsiet bargākā tiesā,
1ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ብዙዎቹ አስተማሪዎች አይሁኑ፥ የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል ታውቃላችሁና።
2Jo mēs visi daudz grēkojam. Kas vārdā neapgrēkojas, tas ir pilnīgs vīrs, jo viņš ir spējīgs savaldīt arī visu miesu.
2ሁላችን በብዙ ነገር እንሰናከላለንና፤ በቃል የማይሰናከል ማንም ቢኖር እርሱ ሥጋውን ሁሉ ደግሞ ሊገታ የሚችል ፍጹም ሰው ነው።
3Ja mēs zirgiem liekam laužņus mutē, lai tie mums paklausītu, tad mēs valdām arī visu viņu ķermeni.
3እነሆ፥ ፈረሶች ይታዘዙልን ዘንድ ልጓም በአፋቸው ውስጥ እናገባለን፥ ሥጋቸውንም ሁሉ እንመራለን።
4Lūk, arī kuģus, lai gan tie ir lieli, un brāzmaini vēji tos mētā, sīka stūre vada, kurp vien vēlas vadītājs.
4እነሆ፥ መርከቦች ደግሞ ይህን ያህል ታላቅ ቢሆኑ በዐውሎ ነፋስም ቢነዱ፥ የመሪ ፈቃድ ወደሚወደው ስፍራ እጅግ ታናሽ በሆነ መቅዘፊያ ይመራሉ።
5Tāpat arī mēle ir mazs loceklis, bet veic lielas lietas. Lūk, cik maza uguns aizdedzina lielu mežu!
5እንዲሁም አንደበት ደግሞ ትንሽ ብልት ሆኖ በታላላቅ ነገር ይመካል። እነሆ፥ ትንሽ እሳት እንዴት ያለ ትልቅ ጫካ ያቃጥላል።
6Arī mēle ir uguns, netaisnības pasaule. Mēle tādā stāvoklī atrodas starp mūsu locekļiem, ka apgāna visu ķermeni un aizdedzina dzīves gājumu, pati būdama elles iededzinātāja.
6አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ በገሃነምም ይቃጠላል።
7Jo visu sugu zvērus un putnus, rāpuļus un pārējos dzīvniekus savalda un ir savaldījusi cilvēka daba.
7የአራዊትና የወፎች የተንቀሳቃሾችና በባሕር ያለ የፍጥረት ወገን ሁሉ በሰው ይገራል፥ ደግሞ ተገርቶአል፤
8Bet mēli neviens cilvēks savaldīt nevar: tā ir nemitīgs ļaunums, pilna nāvīgas indes.
8ነገር ግን አንደበትን ሊገራ ማንም ሰው አይችልም፤ የሚገድል መርዝ የሞላበት ወላዋይ ክፋት ነው።
9Ar to mēs godinām Kungu un Tēvu, un ar to lādam cilvēkus, kas radīti pēc Dieva līdzības.
9በእርሱ ጌታንና አብን እንባርካለን፤ በእርሱም እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠሩትን ሰዎች እንረግማለን፤
10No tās pašas mutes nāk svētība un lāsts. Tas tā, mani brāļi, nedrīkst notikt!
10ከአንድ አፍ በረከትና መርገም ይወጣሉ። ወንድሞቼ ሆይ፥ ይህ እንዲህ ሊሆን አይገባም።
11Vai avots arī izverd no viena un tā paša atvara saldu un rūgtu ūdeni?
11ምንጭስ ከአንድ አፍ የሚጣፍጥንና የሚመርን ውኃ ያመነጫልን?
12Vai, mani brāļi, vīģes koks dod vīnogas un vīnkoks vīģes? Tāpat arī sālsavots nevar dot saldenu ūdeni.
12ወንድሞቼ ሆይ፥ በለስ ወይራን ወይስ ወይን በለስን ልታፈራ ትችላለችን? ከጨው ውኃም ጣፋጭ ውኃ አይወጣም።
13Kas no jums gudrs un saprātīgs, tas lai, pareizi dzīvodams, rāda savus darbus, darītus gudrā lēnprātībā!
13ከእናንተ ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው? በመልካም አንዋዋሩ ስራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ።
14Bet ja savā sirdī nesat rūgtu skaudību un ķildas, tad nelielieties un nemelojiet pret patiesību!
14ነገር ግን መራራ ቅንዓትና አድመኛነት በልባችሁ ቢኖርባችሁ፥ አትመኩ በእውነትም ላይ አትዋሹ።
15Tāda gudrība nenāk no augšienes, bet tā ir pasaulīga, dzīvnieciska, velnišķīga.
15ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፤ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው፥ የአጋንንትም ነው፤
16Jo kur skaudība un ķildas, tur nekārtība un viss ļaunums.
16ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና።
17Tā gudrība, kas nāk no augšienes, ir vispirms šķīsta, pēc tam miermīlīga, pieklājīga, padevīga, labvēlīga labam, pilna žēlsirdības un labu augļu, netiesātāja, neliekuļota.
17ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፥ በኋላም ታራቂ፥ ገር፥ እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት።
18Bet taisnības auglis mierā tiek sēts miera veicinātājos.
18የጽድቅም ፍሬ ሰላምን ለሚያደርጉት ሰዎች በሰላም ይዘራል።