Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

James

4

1No kurienes kari un strīdi jūsu starpā? Vai ne no turienes, no jūsu kārībām, kas karo jūsu locekļos?
1በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ከምቾቶቻችሁ አይደሉምን?
2Jūs iekārojat, bet jums nav; jūs slepkavojat un ienīstat, bet nevarat iegūt; jūs strīdaties un karojat, bet jums nav, jo jūs nelūdzat Dievu.
2ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱም ትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም፤
3Jūs lūdzat, bet nesaņemat, jo jūs ļauni lūdzat, lai to izlietotu savām kārībām.
3ትለምናላችሁ፥ በምቾቶቻችሁም ትከፍሉ ዘንድ በክፉ ትለምናላችሁና አትቀበሉም።
4Jūs, laulības pārkāpēji! Vai jūs nezināt, ka šīs pasaules draudzība ir ienaidā ar Dievu? Un kas gribētu būt šīs pasaules draugs, tas paliek Dievam ienaidnieks.
4አመንዝሮች ሆይ፥ ዓለምን መውደድ ለእግዚአብሔር ጥል እንዲሆን አታውቁምን? እንግዲህ የዓለም ወዳጅ ሊሆን የሚፈቅድ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል።
5Vai jūs domājat, ka Raksti veltīgi saka: Līdz greizsirdībai iekāro gars, kas mājo jūsos?
5ወይስ መጽሐፍ። በእኛ ዘንድ ያሳደረው መንፈስ በቅንዓት ይመኛል ያለው በከንቱ እንደ ተናገረ ይመስላችኋልን?
6Bet Viņš dod lielāku žēlastību; tādēļ sacīts: Dievs pretojas lepniem, bet pazemīgiem dod žēlastību (Sak 3,34)
6ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ። እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል።
7Tādēļ esiet padevīgi Dievam, un pretojieties velnam, un tas bēgs no jums.
7እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤
8Tuvojieties Dievam, un Viņš tuvosies jums. Šķīstījiet rokas, grēcinieki, un tīriet savas sirdis, jūs, dalītie dvēselē!
8ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ።
9Sajūtiet savu niecību, sērojiet un raudiet; jūsu smiekli lai pārvēršas sērās, bet jūsu prieks - skumjās!
9ተጨነቁና እዘኑ አልቅሱም፤ ሳቃችሁ ወደ ኀዘን ደስታችሁም ወደ ትካዜ ይለወጥ።
10Pazemojieties Kunga priekšā, tad Viņš jūs paaugstinās.
10በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ ከፍ ከፍም ያደርጋችኋል።
11Neaprunājiet, brāļi, cits citu! Kas savu brāli aprunā vai savu brāli tiesā, tas aprunā likumu un tiesā likumu. Bet ja tu likumu tiesā, tad tu neesi likuma pildītājs, bet tiesātājs.
11ወንድሞች ሆይ፥ እርስ በርሳችሁ አትተማሙ። ወንድሙን የሚያማ በወንድሙም የሚፈርድ ሕግን ያማል በሕግም ይፈርዳል፤ በሕግም ብትፈርድ ፈራጅ ነህ እንጂ ሕግን አድራጊ አይደለህም።
12Viens ir Likumdevējs un Tiesātājs, kas var pazudināt un glābt.
12ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ነው፤ እርሱም ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው፤ በሌላው ግን የምትፈርድ አንተ ማን ነህ?
13Bet kas tu esi, kas tiesā tuvāko? Lūk, jūs, kas sakāt: Šodien vai rīt mēs dosimies uz to pilsētu un pavadīsim tur kādu gadu, tirgosimies un gūsim peļņu.
13አሁንም። ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና።
14Jūs neziniet, kas būs rīt.
14ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና።
15Jo kas ir jūsu dzīve? Garaiņi, kas īsu brīdi redzami un tad izzūd. Tai vietā jums būtu jāsaka: Ja Kungam labpatiksies un dzīvi būsim, tad darīsim to vai citu.
15በዚህ ፈንታ። ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።
16Bet tagad jūs savā augstprātībā lielaties. Katra tāda lielība ir ļauna.
16አሁን ግን በትዕቢታችሁ ትመካላችሁ፤ እንደዚህ ያለ ትምክህት ሁሉ ክፉ ነው።
17Kas zina labu darīt, bet to nedara, tam ir grēks.
17እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው።