Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

James

5

1Klausieties, bagātie, raudiet un vaimanājiet par tām nelaimēm, kas jums tuvojas!
1አሁንም እናንተ ባለ ጠጎች፥ ስለሚደርስባችሁ ጭንቅ ዋይ ዋይ እያላችሁ አልቅሱ።
2Jūsu bagātība ir sapuvusi un jūsu drēbes ir saēdušas kodes.
2ሀብታችሁ ተበላሽቶአል፥ ልብሳችሁም በብል ተበልቶአል።
3Jūsu zelts un sudrabs ir sarūsējis, un to rūsa būs liecība pret jums un saēdīs jūsu miesas kā uguns. Jūs esat sev sakrājuši dusmas pēdējās dienās.
3ወርቃችሁም ብራችሁም ዝጎአል፥ ዝገቱም ምስክር ይሆንባችኋል ሥጋችሁንም እንደ እሳት ይበላል። ለኋለኛው ቀን መዝገብን አከማችታችኋል።
4Lūk, alga, atrauta strādniekiem, kas nopļāva jūsu laukus, sauc; un viņu saucieni sasnieguši Kunga Sabaota ausis.
4እነሆ፥ እርሻችሁን ያጨዱት የሠራተኞች ደመወዝ በእናንተ ተቀምቶ ይጮኻል፥ የአጫጆችም ድምፅ ወደ ጌታ ፀባዖት ጆሮ ገብቶአል።
5Virs zemes jūs dzīrojāt un savas sirdis barojāt izpriecām kaujamai dienai.
5በምድር ላይ ተቀማጥላችኋል በሴሰኝነትም ኖራችኋል፤ ለእርድ ቀን እንደሚያወፍር ልባችሁን አወፍራችኋል።
6Jūs notiesājāt un nonāvējāt Taisnīgo, un Viņš jums nepretojās.
6ጻድቁን ኰንናችሁታል ገድላችሁትማል፤ እናንተን አይቃወምም።
7Esiet pacietīgi, brāļi, līdz Kunga atnākšanai! Lūk, zemkopis gaida dārgo zemes augli, pacietīgi ilgodamies, kamēr tas saņems agro un vēlo lietu.
7እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ታገሡ። እነሆ፥ ገበሬው የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ እስኪቀበል ድረስ እርሱን እየታገሠ የከበረውን የመሬት ፍሬ ይጠብቃል።
8Tāpēc arī jūs esiet pacietīgi un stipriniet savas sirdis, jo Kunga atnākšana ir tuvu!
8እናንተ ደግሞ ታገሡ፥ ልባችሁንም አጽኑ፤ የጌታ መምጣት ቀርቦአልና።
9Negaudieties, brāļi, viens par otru, lai netiktu tiesāti! Lūk, tiesnesis stāv durvju priekšā!
9ወንድሞች ሆይ፥ እንዳይፈረድባችሁ እርስ በርሳችሁ አታጉረምርሙ፤ እነሆ፥ ፈራጅ በደጅ ፊት ቆሞአል።
10Brāļi, neveiksmēs, ciešanās un pacietībai ņemiet priekšzīmi no praviešiem, kas runāja Kunga vārdā.
10ወንድሞች ሆይ፥ የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ።
11Lūk, mēs teicam svētīgus tos, kas izcietuši. Jūs dzirdējāt, par Ījaba pacietību un redzējāt, kāds bija Kunga gala mērķis, jo Kungs ir žēlsirdīgs un apžēlotājs.
11እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደ ፈጸመለት አይታችኋል፤ ጌታ እጅግ የሚምር የሚራራም ነውና።
12Vispirms, mani brāļi, nezvēriet ne pie debesīm, ne pie zemes, ne citu kādu zvērestu. Jūsu runai jābūt: jā-jā, nē-nē, lai jūs netiktu tiesāti.
12ከሁሉም በፊት፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ በሰማይ ቢሆን በምድርም ቢሆን በሌላ መሐላም ቢሆን በምንም አትማሉ፤ ነገር ግን ከፍርድ በታች እንዳትወድቁ ነገራችሁ አዎን ቢሆን አዎን ይሁን፥ አይደለምም ቢሆን አይደለም ይሁን።
13Ja kāds no jums skumst, lai lūdz Dievu! Ja kādam labs prāts, tas lai dzied psalmus!
13ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር እርሱ ይዘምር።
14Ja kāds no jums slimo, lai tas aicina Baznīcas priesterus, lai tie par viņu lūdz Dievu, svaidīdami ar eļļu Kunga vārdā!
14ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት።
15Un ticīgā lūgšana izglābs slimnieku, un Kungs viņu pacels; un, ja viņš būtu grēkojis viņam tiks piedots.
15የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል።
16Izsūdziet cits citam savus grēkus un lūdziet Dievu cits par citu, lai tiktu pestīti, jo daudz spēj neatlaidīga, taisnīga lūgšana!
16እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።
17Elijs bija mums līdzīgs cilvēks, padots ciešanām. Tas sirsnīgi lūdza Dievu, lai lietus nelītu, un nelija virs zemes trīs gadus un sešus mēnešus.
17ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
18Un atkal viņš lūdza Dievu, un debess deva lietu, un zeme nesa savus augļus. (3 Ķēn 17,1; 18,45)
18ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች።
19Mani brāļi, ja kāds no jums nomaldīsies no patiesības, un kāds viņu atgriež,
19ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ማንም ከእውነት ቢስት አንዱም ቢመልሰው፥
20Lai tas, kas atgriezis grēcinieku no viņa maldu ceļa, zina, ka izglābs tā dvēseli no nāves un segs daudz grēku.
20ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ።