1Tad Pilāts ņēma un šaustīja Jēzu.
1በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው።
2Un kareivji, nopinuši ērkšķu kroni, uzlika to Viņam galvā un aplika Viņam purpura virsdrēbes.
2ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤
3Un tie nāca pie Viņa un sacīja: Esi sveicināts, jūdu Ķēniņ, un sita Viņam vaigā.
3እየቀረቡም። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤
4Tad Pilāts atkal izgāja ārā un sacīja viņiem: Lūk, es Viņu izvedu pie jums ārā, lai jūs atzītu, ka es pie Viņa nekādas vainas neatrodu.
4በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም ደግሞ ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ አላቸው።
5Tad Jēzus iznāca ērkšķu kronī un purpura virsdrēbēs. Un viņš tiem sacīja: Lūk, kāds Cilvēks!
5ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ።
6Kad augstie priesteri un kalpi ieraudzīja Viņu, tie kliedza, sacīdami: Sit Viņu krustā, sit Viņu krustā! Pilāts viņiem sacīja: Ņemiet jūs Viņu un sitiet krustā, jo es pie Viņa vainas neatrodu!
6ጲላጦስም። እነሆ ሰውዬው አላቸው። የካህናት አለቆችና ሎሌዎች ባዩትም ጊዜ። ስቀለው ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኘሁበትምና እናንተ ወስዳችሁ ስቀሉት አላቸው።
7Jūdi viņam atbildēja: Mums ir likums un pēc likuma Viņam jāmirst, jo Viņš sevi darījis par Dieva Dēlu.
7አይሁድም መልሰው። እኛ ሕግ አለን፥ እንደ ሕጋችንም ሊሞት ይገባዋል፥ ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ አድርጎአልና አሉት።
8Pilāts, dzirdēdams šos vārdus, vēl vairāk nobijās.
8ስለዚህ ጲላጦስ ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እግጅ ፈራ፤
9Un viņš, atkal iegājis tiesas namā, sacīja Jēzum: No kurienes Tu esi? Bet Jēzus nedeva vīņam atbildi.
9ተመልሶም ወደ ገዡ ግቢ ገባና ኢየሱስን። አንተ ከወዴት ነህ? አለው። ኢየሱስ ግን አንድ እንኳ አልመለሰለትም።
10Tad Pilāts sacīja Viņam: Tu man neatbildi? Vai Tu nezini, ka man vara Tevi krustā sist un vara Tevi atlaist?
10ስለዚህ ጲላጦስ። አትነግረኝምን? ልሰቅልህ ሥልጣን እንዳለኝ ወይም ልፈታህ ሥልጣን እንዳለኝ አታውቅምን? አለው።
11Jēzus atbildēja: Tev nebūtu nekādas varas pār mani, ja tā nebūtu tev dota no augšienes. Tāpēc tam, kas mani tev nodeva, lielāks grēks.
11ኢየሱስም መልሶ። ከላይ ካልተሰጠህ በቀር በእኔ ላይ ምንም ሥልጣን ባልነበረህም፤ ስለዚህ ለአንተ አሳልፎ የሰጠኝ ኃጢአቱ የባሰ ነው አለው።
12Un no šī laika Pilāts meklēja Viņu atlaist. Bet jūdi kliedza, sacīdami: Ja tu Viņu atlaid, tu neesi ķeizara draugs, jo ikviens, kas sevi ceļ par ķēniņu, pretojas ķeizaram.
12ከዚህ በኋላ ጲላጦስ ሊፈታው ፈለገ፤ ነገር ግን አይሁድ። ይህንስ ብትፈታው የቄሣር ወዳጅ አይደለህም፤ ራሱን ንጉሥ የሚያደርግ ሁሉ የቄሣር ተቃዋሚ ነው እያሉ ጮኹ።
13Bet Pilāts, dzirdēdams šos vārdus, izveda Jēzu ārā un sēdās soģa krēslā tanī vietā, kas saucās Litostrotos, ebrejiski Gabata.
13ጲላጦስም ይህን ነገር ሰምቶ ኢየሱስን ወደ ውጭ አወጣው፥ በዕብራይስጥም ገበታ በተባለው ጸፍጸፍ በሚሉት ስፍራ በፍርድ ወንበር ተቀመጠ።
14Bija sagatavošanās diena pirms Lieldienām ap sesto stundu. Un viņš sacīja jūdiem: Lūk, jūsu ķēniņš!
14ለፋሲካም የማዘጋጀት ቀን ነበረ፤ ስድስት ሰዓትም የሚያህል ነበረ፤ አይሁድንም። እነሆ ንጉሣችሁ አላቸው።
15Bet tie kliedza: Nost, nost! Sit Viņu krustā! Pilāts sacīja viņiem: Jūsu ķēniņu lai situ krustā? Augstie priesteri atbildēja: Mums nav ķēniņa, tik vienīgi ķeizars!
15እነርሱ ግን። አስወግደው፥ አስወግደው፥ ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። ንጉሣችሁን ልስቀለውን? አላቸው። የካህናት አለቆችም። ከቄሣር በቀር ሌላ ንጉሥ የለንም ብለው መለሱለት።
16Tad viņš atdeva tiem Viņu krustā sišanai. Bet tie paņēma Jēzu un aizveda.
16ስለዚህ በዚያን ጊዜ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጣቸው።
17Un Viņš, nesdams savu krustu, gāja uz to vietu, kas saucās Kalvārija, bet ebrejiski Golgota.
17ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ።
18Tur tie piesita Viņu krustā un līdz ar Viņu abās pusēs citus divus, bet Jēzu vidū.
18በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።
19Bet Pilāts uzrakstīja arī uzrakstu un uzlika krustā. Un uzrakstīts bija: Jēzus Nācarietis, jūdu Ķēniņš.
19ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ።
20Šo uzrakstu lasīja daudzi jūdi, jo vieta, kur Jēzus bija krustā piesists, bija tuvu pilsētai; un rakstīts bija ebrejiski, grieķiski un latīniski.
20ኢየሱስም የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ነበረና ከአይሁድ ብዙዎች ይህን ጽሕፈት አነበቡት፤ በዕብራይስጥና በሮማይስጥ በግሪክም ተጽፎ ነበር።
21Tad jūdu augstie priesteri sacīja Pilātam: Neraksti: jūdu Ķēniņš, bet ka Viņš pats sacīja: Es esmu jūdu Ķēniņš.
21ስለዚህ የአይሁድ ካህናት አለቆች ጲላጦስን። እርሱ። የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ አሉት።
22Pilāts atbildēja: Ko uzrakstīju, to uzrakstīju.
22ጲላጦስም። የጻፍሁትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ።
23Tad kareivji, piesituši Viņu krustā, paņēma Viņa drēbes (un sadalīja četrās daļās, katram kareivim pa daļai) un svārkus. Bet svārki nebija šūti: tie bija viscaur austi.
23ጭፍሮችም ኢየሱስን በሰቀሉት ጊዜ ልብሶቹን ወስደው ለእያንዳንዱ ጭፍራ አንድ ክፍል ሆኖ በአራት ከፋፈሉት፤ እጀጠባቡን ደግሞ ወሰዱ። እጀ ጠባቡም ከላይ ጀምሮ ወጥ ሆኖ የተሠራ ነበረ እንጂ የተሰፋ አልነበረም።
24Tad tie viens otram sacīja: Nedalīsim tos, bet metīsim kauliņus, kam tie būs. Tā piepildījās, kas teikts Rakstos: viņi sadalīja savā starpā manas drēbes, bet par maniem svārkiem meta kauliņus. Tā kareivji to padarīja. (Ps.21,19)
24ስለዚህ እርስ በርሳቸው። ለማን እንዲሆን በእርሱ ዕጣ እንጣጣልበት እንጂ አንቅደደው ተባባሉ። ይህም። ልብሴን እርስ በርሳቸው ተከፋፈሉ በእጀ ጠባቤም ዕጣ ተጣጣሉበት የሚለው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።
25Bet pie Jēzus krusta stāvēja Viņa māte un Viņa mātes māsa Marija, Kleofasa sieva, un Marija Magdalēna.
25ጭፍሮችም እንዲህ አደረጉ። ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ የእናቱም እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።
26Tad Jēzus, redzēdams māti un mācekli, ko Viņš mīlēja, stāvam, sacīja savai mātei: Sieviet, lūk, tavs dēls!
26ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን። አንቺ ሴት፥ እነሆ ልጅሽ አላት።
27Pēc tam Viņš sacīja māceklim: Lūk, tava māte! Un no tās stundas māceklis ņēma viņu pie sevis.
27ከዚህ በኋላ ደቀ መዝሙሩን። እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት።
28Pēc tam Jēzus, zinādams, ka viss padarīts, lai piepildītos Raksti, sacīja: Slāpstu!
28ከዚህ በኋላ ኢየሱስ አሁን ሁሉ እንደተፈጸመ አውቆ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ። ተጠማሁ አለ።
29Tur bija nolikts trauks, pilns etiķa. Tad kareivji etiķī piesūcināja sūkli, uzsprauda izapa stiebrā un pacēla pie Viņa mutes.
29በዚያም ሆምጣጤ የሞላበት ዕቃ ተቀምጦ ነበር፤ እነርሱም ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው በሁሶፕም አድርገው ወደ አፉ አቀረቡለት።
30Kad Jēzus etiķi bija baudījs, Viņš sacīja: Ir izpildīts! Un Viņš, galvu noliecis, atdeva garu.
30ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።
31Bet tā kā bija sagatavošanās diena, tad jūdi, lai miesas sabatā nepaliktu krustā, jo tā bija lielā sabata diena, lūdza Pilātu, lai viņu stilbkauli tiktu salauzti un tos noņemtu.
31አይሁድም የማዘጋጀት ቀን ስለ ሆነ ያ ሰንበት ትልቅ ነበረና ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር፥ ጭናቸውን ሰብረው እንዲያወርዱአቸው ጲላጦስን ለመኑት።
32Tad atnāca kareivji un pirmajam un otrajam, kas kopā ar Viņu bija piesisti krustā, salauza stilbkaulus.
32ጭፍሮችም መጥተው የፊተኛውን ጭን ከእርሱም ጋር የተሰቀለውን የሌላውን ጭን ሰበሩ፤
33Bet kad viņi nogāja pie Jēzus un redzēja, ka Viņš jau miris, tie nelauza Viņa stilbkaulus,
33ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፤
34Bet viens no kareivjiem ar šķēpu atvēra Viņa sānus, un tūdaļ iztecēja asinis un ūdens.
34ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ።
35Un tas, kas to redzēja, deva liecību, un viņa liecība patiesa. Un viņš zina, ka runā patiesību, lai arī jūs ticētu.
35ያየውም መስክሮአል፤ ምስክሩም እውነት ነው፤ እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል።
36Jo tas notika, lai izpildītos Raksti: nevienu kaulu Viņam nebūs salauzt. (2.Moz.12,46)
36ይህ የሆነ። ከእርሱ አጥንት አይሰበርም የሚል የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው።
37Un arī citi Raksti saka: Tie skatīs Viņu, ko tie pārdūruši. (Zah.12,10)
37ደግሞም ሌላው መጽሐፍ። የወጉትን ያዩታል ይላል።
38Bet pēc tam Jāzeps no Arimatejas (tāpēc ka viņš bija Jēzus māceklis, bet slepenībā aiz bailēm no jūdiem) lūdza Pilātu, lai atļauj noņemt Jēzus miesas un Pilāts atļāva. Tad viņš nāca un noņēma Jēzus miesas.
38ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ።
39Bet arī Nikodēms atnāca, kas agrāk bija nācis pie Jēzus naktī, un atnesa kādas simts mārciņas mirru un aloes maisījumu.
39ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ።
40Tad viņi paņēma Jēzus miesas un satina tās audeklā kopā ar smaržām, kā tas bija parasts, jūdus apbedījot.
40የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።
41Bet tanī vietā, kur Viņš tika krustā piesists, bija dārzs un dārzā jauns kaps, kurā vēl neviens nebija guldīts.
41በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።
42Jūdu sagatavošanās dienas dēļ tur viņi guldīja Jēzu, jo kaps bija tuvu.
42ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት።