Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

John

20

1Pirmajā nedēļas dienā, rīta agrumā, kad vēl bija tumsa, Marija Magdalēna atnāca pie kapa un redzēja akmeni noveltu no kapa.
1ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች።
2Tad viņa skriešus devās pie Sīmaņa Pētera un pie otra mācekļa, ko Jēzus mīlēja, un sacīja viņiem: Viņi Kungu no kapa paņēmuši, un mēs nezinām, kur tie Viņu nolikuši.
2እየሮጠችም ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ወደ ሌላው ደቀ መዝሙር መጥታ። ጌታን ከመቃብር ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አናውቅም አለቻቸው።
3Tad Pēteris un otrs māceklis izgāja un atnāca pie kapa.
3ስለዚህ ጴጥሮስና ሌላው ደቀ መዝሙር ወጥተው ወደ መቃብሩ ሄዱ።
4Abi viņi skrēja reizē; bet otrs māceklis skrēja ātrāk nekā Pēteris un nonāca pie kapa pirmais.
4ሁለቱም አብረው ሮጡ፤ ሌላው ደቀ መዝሙርም ከጴጥሮስ ይልቅ ፈጥኖ ወደ ፊት ሮጠና አስቀድሞ ከመቃብሩ ደረሰ፤
5Un viņš noliecās un redzēja noliktu audeklu, tomēr iekšā negāja.
5ዝቅም ብሎ ቢመለከት የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ነገር ግን አልገባም።
6Tad, viņam sekodams, atnāca Sīmanis Pēteris, iegāja kapā un redzēja noliktu audeklu.
6ስምዖን ጴጥሮስም ተከትሎት መጣ ወደ መቃብሩም ገባ፤ የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥
7Un sviedrauts, kas bijis uz Viņa galvas, nebija nolikts pie audekla, bet atsevišķi satīts savā vietā.
7ደግሞም በራሱ የነበረውን ጨርቅ ለብቻው በአንድ ስፍራ ተጠምጥሞ እንደ ነበረ እንጂ ከተልባ እግሩ ልብስ ጋር ተቀምጦ እንዳልነበረ አየ።
8Tad iegāja arī tas māceklis, kas pirmais atnāca pie kapa un redzēja un ticēja.
8በዚያን ጊዜ አስቀድሞ ወደ መቃብር የመጣውም ሌላው ደቀ መዝሙር ደግሞ ገባ፥ አየም፥ አመነም፤
9Jo viņi vēl neizprata Rakstus, ka Viņam vajadzēja no miroņiem augšāmcelties.
9ከሙታን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው የሚለውን የመጽሐፉን ቃል ገና አላወቁም ነበርና።
10Tad mācekļi atkal atgriezās savā mītnē.
10ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቤታቸው ደግሞ ሄዱ።
11Bet Marija stāvēja ārā pie kapa un raudāja. Un, vēl raudādama, viņa noliecās un paskatījās kapā.
11ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተ ውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመለከተች፤
12Un viņa redzēja divus eņģeļus baltās drānās sēžam: vienu galvgalī un otru kājgalī, kur bija novietotas Jēzus miesas.
12ሁለት መላእክትም ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት በነበረው አንዱ በራስጌ ሌላውም በእግርጌ ተቀምጠው አየች።
13Viņi tai sacīja: Sieviet, ko tu raudi? Viņa tiem sacīja: Tāpēc, ka tie manu Kungu aiznesuši, un es nezinu, kur tie Viņu likuši.
13እነርሱም። አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? አሉአት። እርስዋም። ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው።
14To sacījusi, viņa pagriezās atpakaļ un redzēja Jēzu stāvam, bet nezināja, ka tas Jēzus.
14ይህንም ብላ ወደ ኋላ ዘወር ስትል ኢየሱስን ቆሞ አየችው፤ ኢየሱስም እንደ ሆነ አላወቀችም።
15Jēzus sacīja viņai: Sieviet, ko raudi? Ko tu meklē? Tā, domādama, ka tas dārznieks, sacīja Viņam: Kungs, ja tu Viņu aiznesi, tad saki man, kur tu Viņu liki, un es Viņu paņemšu.
15ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? ማንንስ ትፈልጊያለሽ? አላት። እርስዋም የአትክልት ጠባቂ መስሎአት። ጌታ ሆይ፥ አንተ ወስደኸው እንደ ሆንህ ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ እኔም እወስደዋለሁ አለችው።
16Jēzus sacīja viņai: Marija! Tā apgriezās un sacīja Viņam: Rabboni! kas nozīmē: Mācītāj!
16ኢየሱስም። ማርያም አላት። እርስዋ ዘወር ብላ በዕብራይስጥ። ረቡኒ አለችው፤ ትርጓሜውም። መምህር ሆይ ማለት ነው።
17Jēzus sacīja viņai: Nepieskaries man, jo es vēl neesmu aizgājis pie sava Tēva, bet ej pie maniem brāļiem un saki viņiem: es aizeju pie sava Tēva un jūsu Tēva, pie sava Dieva un jūsu Dieva.
17ኢየሱስም። ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ። እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።
18Tad Marija Magdalēna aizgāja un paziņoja mācekļiem: Es redzēju Kungu, un to Viņš man pateica.
18መግደላዊት ማርያም መጥታ ጌታን እንዳየች ይህንም እንዳላት ለደቀ መዛሙርቱ ነገረች።
19Kad tanī pat pirmajā nedēļas dienā, vakaram iestājoties, aiz bailēm no jūdiem durvis, kur mācekļi bija sapulcējušies, bija aizslēgtas, Jēzus atnāca un nostājās viņu vidū, un sacīja tiem: Miers jums!
19ያም ቀን እርሱም ከሳምንቱ ፊተኛው በመሸ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ተሰብስበው በነበሩበት፥ አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹ ተዘግተው ሳሉ፥ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።
20Un Viņš, to pateicis, tiem rādīja rokas un sānus. Tad mācekļi, redzēdami Kungu, kļuva līksmi.
20ይህንም ብሎ እጆቹንም ጎኑንም አሳያቸው። ደቀ መዛሙርቱም ጌታን ባዩ ጊዜ ደስ አላቸው።
21Tad Viņš atkal tiem sacīja: Miers jums! Kā mans Tēvs sūtījis mani, tā es jūs sūtu.
21ኢየሱስም ዳግመኛ። ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እንደ ላከኝ እኔ ደግሞ እልካችኋለሁ አላቸው።
22To pateicis, Viņš dvesa un sacīja tiem: Saņemiet Svēto Garu!
22ይህንም ብሎ እፍ አለባቸውና። መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
23Kam jūs grēkus piedosiet, tiem tie būs piedoti, kam tos aizturēsiet, tiem tie būs aizturēti.
23ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል አላቸው።
24Bet Toms, viens no tiem divpadsmit, saukts Dvīnis, nebija pie viņiem, kad atnāca Jēzus.
24ነገር ግን ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ኢየሱስ በመጣ ጊዜ ከእነርሱ ጋር አልነበረም።
25Tad pārējie mācekļi sacīja viņam: Mēs redzējām Kungu. Bet viņš sacīja tiem: Ja es neredzēšu naglu rētas Viņa rokās un savu pirkstu neielikšu naglu rētās, un savu roku neielikšu Viņa sānos, es neticēšu.
25ሌሎቹም ደቀ መዛሙርቱ። ጌታን አይተነዋል አሉት። እርሱ ግን። የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም አላቸው።
26Un pēc astoņām dienām atkal Viņa mācekļi un arī Toms bija iekšā. Un durvis bija aizslēgtas. Jēzus atnāca un nostājās starp viņiem, un sacīja: Miers jums!
26ከስምንት ቀን በኋላም ደቀ መዛሙርቱ ደግመው በውስጥ ነበሩ፥ ቶማስም ከእነርሱ ጋር ነበረ። ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።
27Pēc tam Viņš sacīja Tomam: Sniedz šurp savu pirkstu un aplūko manas rokas, un sniedz šurp savu roku un liec to manos sānos, un neesi neticīgs, bet ticīgs!
27ከዚያም በኋላ ቶማስን። ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለው።
28Toms atbildēja Viņam, sacīdams: Mans Kungs un mans Dievs!
28ቶማስም። ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት።
29Jēzus sacīja viņam: Tom, tu ticēji tāpēc, ka tu mani redzēji. Svētīgi tie, kas nav redzējuši, bet ir ticējuši.
29ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው።
30Vēl daudz citus brīnumus Jēzus darīja savu mācekļu priekšā, kas nav rakstīti šinī grāmatā.
30ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤
31Bet šis ir rakstīts, lai jūs ticētu, ka Jēzus ir Kristus, Dieva Dēls, un lai jūs ticēdami iemantotu dzīvību Viņa vārdā.
31ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።