Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

John

21

1Pēc tam Jēzus atkal parādījās mācekļiem pie Tibērijas jūras. Viņš parādījās tā:
1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በጥብርያዶስ ባሕር አጠገብ ለደቀ መዛሙርቱ እንደ ገና ተገለጠላቸው፤
2Tur bija kopā Sīmanis Pēteris un Toms, saukts Dvīnis, un Natanaēls, kas bija no Galilejas Kānas, un Zebedeja dēli, un vēl citi divi no Viņa mācekļiem.
2እንዲህም ተገለጠ። ስምዖን ጴጥሮስና ዲዲሞስ የሚባለው ቶማስ ከገሊላ ቃና የሆነ ናትናኤልም የዘብዴዎስም ልጆች ከደቀ መዛሙርቱም ሌሎች ሁለት በአንድነት ነበሩ።
3Sīmanis Pēteris sacīja viņiem: Es eju zvejot. Tie sacīja viņam: Arī mēs iesim tev līdz. Un viņi izgāja un iekāpa laivā, bet tanī naktī nekā neieguva.
3ስምዖን ጴጥሮስ። ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ አላቸው። እነርሱም። እኛም ከአንተ ጋር እንመጣለን አሉት። ወጥተውም ወደ ታንኳይቱ ገቡ በዚያችም ሌሊት ምንም እላጠመዱም።
4Bet rīta ausmā Jēzus stāvēja krastā; tomēr mācekļi nepazina, ka tas ir Jēzus.
4በነጋም ጊዜ ኢየሱስ በባሕር ዳር ቆመ፤ ደቀ መዛሙርቱ ግን ኢየሱስ መሆኑን አላወቁም።
5Tad Jēzus viņiem sacīja: Bērni, vai jums ir kas ēdams? Tie atbildēja Viņam: Nav!
5ኢየሱስም። ልጆች ሆይ፥ አንዳች የሚበላ አላችሁን? አላቸው። የለንም ብለው መለሱለት።
6Viņš tiem sacīja: Izmetiet tīklu laivas labajā pusē un jūs atradīsiet. Tad viņi izmeta un vairs nespēja to pavilkt zivju daudzuma dēļ.
6እርሱም። መረቡን በታንኳይቱ በስተ ቀኝ ጣሉት ታገኙማላችሁ አላቸው። ስለዚህ ጣሉት፤ በዚህም ጊዜ ከዓሣው ብዛት የተነሣ ሊጐትቱት አቃታቸው።
7Tad māceklis, ko Jēzus mīlēja, sacīja Pēterim: Tas ir Kungs! Sīmanis Pēteris, dzirdēdams, ka tas ir Kungs, apjoza virsdrēbes (jo bija izģērbies) un metās jūrā.
7ኢየሱስ ይወደው የነበረውም ደቀ መዝሙር ጴጥሮስን። ጌታ እኮ ነው አለው። ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ ጌታ መሆኑን በሰማ ጊዜ ዕራቁቱን ነበረና ልብሱን ታጥቆ ወደ ባሕር ራሱን ጣለ።
8Bet citi mācekļi brauca laivā, vilkdami tīklu ar zivīm (jo tie nebija tālu no krasta, bet tikai apmēram divsimt olekšu).
8ሌሎቹ ደቀ መዛሙርት ግን ከምድር ሁለት መቶ ክንድ ያህል እንጂ እጅግ አልራቁም ነበርና ዓሣ የሞላውን መረብ እየሳቡ በጀልባ መጡ።
9Kad viņi izkāpa malā, tie redzēja saliktas ogles, bet virs tām uzliktu zivi un maizi.
9ወደ ምድርም በወጡ ጊዜ ፍምና ዓሣ በላዩ ተቀምጦ እንጀራም አዩ።
10Jēzus sacīja viņiem: Atnesiet no tām zivīm, ko jūs tagad ieguvāt!
10ኢየሱስም። አሁን ካጠመዳችሁት ዓሣ አምጡ አላቸው።
11Tad Sīmanis Pēteris, iekāpis laivā, izvilka krastā pilnu tīklu ar simt piecdesmit trim lielām zivīm. Un, lai gan to bija tik daudz, tīkls nesaplīsa.
11ስምዖን ጴጥሮስም ወደ ጀልባይቱ ገብቶ መቶ አምሳ ሦስት ታላላቅ ዓሦች ሞልቶ የነበረውን መረብ ወደ ምድር ጐተተ፤ ይህንም ያህል ብዙ ሲሆን መረቡ አልተቀደደም።
12Jēzus sacīja viņiem: Nāciet un ēdiet! Un neviens no klātesošajiem neuzdrošinājās Viņam jautāt: Kas Tu esi? Jo viņi zināja, ka tas ir Kungs.
12ኢየሱስም። ኑ፥ ምሳ ብሉ አላቸው። ከደቀ መዛሙርቱ አንድ ስንኳ። አንተ ማን ነህ? ብሎ ሊመረምረው የደፈረ አልነበረም፤ ጌታ መሆኑን አውቀው ነበርና።
13Tad Jēzus nāk, ņem maizi un dod viņiem, un tāpat arī zivi.
13ኢየሱስም መጣና እንጀራ አንሥቶ ሰጣቸው፥ እንዲሁም ዓሣውን።
14Šī jau bija trešā reize, kad Jēzus pēc augšāmcelšanās no miroņiem parādījās saviem mācekļiem.
14ኢየሱስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሲገለጥላቸው ይህ ሦስተኛው ጊዜ ነበረ።
15Kad nu viņi bija paēduši, Jēzus sacīja Sīmanim Pēterim: Sīmani, Jonas dēls, vai tu mani mīli vairāk nekā viņi? Tas Viņam sacīja: Tiešām, Kungs, Tu zini, ka es Tevi mīlu. Viņš sacīja tam: Gani manus jērus!
15ምሳ ከበሉ በኋላም ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ግልገሎቼን አሰማራ አለው።
16Tad Viņš atkal sacīja tam: Sīmani, Jonas dēls, vai tu mani mīli? Tas Viņam sacīja: Tiešām, Kungs, Tu zini, ka es Tevi mīlu! Viņš tam sacīja: Gani manus jērus!
16ደግሞ ሁለተኛ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው።
17Un trešo reizi Viņš tam sacīja: Sīmani, Jonas dēls, vai tu mani mīli? Pēteris noskuma, tāpēc ka Viņš trešo reizi tam sacīja: Vai tu mani mīli? Un tas Viņam sacīja: Kungs, Tu visu zini; Tu zini, ka es Tevi mīlu. Viņš tam sacīja: Gani manas avis!
17ጠቦቶቼን ጠብቅ አለው። ሦስተኛ ጊዜ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። ሦስተኛ። ትወደኛለህን? ስላለው ጴጥሮስ አዘነና። ጌታ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ኢየሱስም። በጎቼን አሰማራ።
18Patiesi, patiesi es tev saku: kad tu biji jauns, tad pats apjozies un gāji, kur vēlējies. Bet kad tu paliksi vecs, tu izstiepsi savas rokas, un citi tevi apjozīs un vedīs, kur tu nevēlies.
18እውነት እውነት እልሃለሁ፥ አንተ ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፥ ሌላውም ያስታጥቅሃል ወደማትወደውም ይወስድሃል አለው።
19Bet to Viņš sacīja, norādīdams, kādā nāvē tas pagodinās Dievu. Un Viņš, to pateicis, sacīja tam: Seko man!
19በምን ዓይነት ሞት እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን አለ። ይህንም ብሎ። ተከተለኝ አለው።
20Pēteris, pagriezies atpakaļ, redzēja to mācekli sekojam, ko Jēzus mīlēja, kas Vakariņās piekļāvās Viņa krūtīm un sacīja: Kungs, kurš ir tas, kas Tevi nodos?
20ጴጥሮስም ዘወር ብሎ ኢየሱስ ይወደው የነበረውን ደቀ መዝሙር ሲከተለው አየ፤ እርሱም ደግሞ በእራት ጊዜ በደረቱ ተጠግቶ። ጌታ ሆይ፥ አሳልፎ የሚሰጥህ ማን ነው? ያለው ነበረ።
21Pēteris to ieraudzījis sacīja Jēzum: Kungs, kas būs ar šo?
21ጴጥሮስም ይህን አይቶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ ይህስ እንዴት ይሆናል? አለው።
22Jēzus sacīja viņam: Tā es vēlos, lai viņš paliek, kamēr es atnāku, kas tev daļas? Tu seko man!
22ኢየሱስም። እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ፥ ምን አግዶህ? አንተ ተከተለኝ አለው።
23Tā šī runa izpaudās starp brāļiem, ka šis māceklis nemirs. Bet Jēzus nesacīja viņam, ka tas nemirs, bet: Tā es vēlos, lai viņš paliek, kamēr atnākšu, kas tev daļas?
23ስለዚህ። ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም የሚለው ይህ ነገር ወደ ወንድሞች ወጣ፤ ነገር ግን ኢየሱስ። እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው እንጂ አይሞትም አላለውም።
24Šis ir tas māceklis, kas par šo liecību dod un uzrakstīja šo; un mēs zinām, ka viņa liecība patiesa.
24ስለ እነዚህም የመሰከረ ይህንንም ጽፎ ያለ ይህ ደቀ መዝሙር ነው፥ ምስክሩም እውነት እንደ ሆነ እናውቃለን።
25Bet vēl ir daudz citu lietu, ko Jēzus darījis. Ja tās atsevišķi uzrakstītu, man šķiet, visa pasaule nespētu aptvert sarakstītās grāmatas.
25ኢየሱስም ያደረገው ብዙ ሌላ ነገር ደግሞ አለ፤ ሁሉ በእያንዳንዱ ቢጻፍ ለተጻፉት መጻሕፍት ዓለም ራሱ ባልበቃቸውም ይመስለኛል።