Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Romans

1

1Pāvils, Jēzus Kristus kalps, aicināts apustulis, izredzēts Dieva evaņģēlijam,
1ሐዋርያ ሊሆን የተጠራ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ጳውሎስ በነቢያቱ አፍ በቅዱሳን መጻሕፍት አስቀድሞ ተስፋ ለሰጠው ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየ።
2Ko Viņš jau iepriekš apsolīja svētajos Rakstos caur praviešiem
3ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
3Par savu Dēlu, kas pēc miesas Viņam cēlies no Dāvida cilts,
5በእርሱም ስለ ስሙ በአሕዛብ ሁሉ መካከል ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን፤
4Kas svētdarītājā Garā ar savu augšāmcelšanos no miroņiem spēkā parādījās Dieva Dēls, mūsu Kungs Jēzus Kristus.
6በእነርሱም መካከል የኢየሱስ ክርስቶስ ልትሆኑ የተጠራችሁ እናንተ ደግሞ ናችሁ።
5Caur Viņu mēs saņēmām žēlastību un apustuļa sūtību pakļaut visas tautas ticībai Viņa vārda dēļ.
7በእግዚአብሔር ለተወደዳችሁና ቅዱሳን ልትሆኑ ለተጠራችሁ በሮሜ ላላችሁት ሁሉ፥ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
6Tanī arī jūs esat Jēzus Kristus aicināti.
8እምነታችሁ በዓለም ሁሉ ስለ ተሰማች አስቀድሜ ስለ ሁላችሁ አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ።
7Visiem Dieva mīļotājiem, aicinātajiem svētajiem Romā: žēlastība jums un miers no Dieva, mūsu Tēva, un no Kunga Jēzus Kristus!
9በልጁ ወንጌል በመንፈሴ የማገለግለው እግዚአብሔር ምስክሬ ነውና፤ ምናልባት ብዙ ቆይቼ ወደ እናንተ አሁን እንድመጣ በእግዚአብሔር ፈቃድ መንገዴን እንዲያቀናልኝ እየለመንሁ ሁልጊዜ ስጸልይ ስለ እናንተ ሳላቋርጥ አሳስባለሁ።
8Vispirms es pateicos Dievam caur Jēzu Kristu par jums visiem, jo jūsu ticība tiek daudzināta visā pasaulē.
11ትጸኑ ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችሁ ላያችሁ እናፍቃለሁና፤
9Jo Dievs, kuram es savā garā Viņa Dēla evaņģēlijā kalpoju, ir mans liecinieks, ka es jūs bez mitēšanās pieminu.
12ይህንም ማለቴ በመካከላችን ባለች በእናንተና በእኔ እምነት አብረን በእናንተ እንድንጽናና ነው።
10Savās lūgšanās, pastāvīgi lūgdams, lai man saskaņā ar Dieva prātu kādreiz kaut kā pašķirtos ceļš aiziet pie jums.
13ወንድሞች ሆይ፥ በሌሎቹ አሕዛብ ደግሞ እንደ ሆነ በእናንተም ፍሬ አገኝ ዘንድ ብዙ ጊዜ ወደ እናንተ ልመጣ እንዳሰብሁ እስከ አሁን ግን እንደ ተከለከልሁ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ።
11Jo es ilgojos jūs redzēt, lai sniegtu jums kādu garīgu žēlastības dāvanu jūsu stiprināšanai,
14ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤
12Tas ir, reizē ar jums gūtu iepriecinājumu savstarpējā ticībā, jūsējā un manējā.
15ስለዚህም በሚቻለኝ መጠን በሮሜ ላላችሁ ለእናንተ ደግሞ ወንጌልን ልሰብክ ተዘጋጅቼአለሁ።
13Bet es, brāļi, negribu atstāt jūs neziņā par to, ka es vairākkārt biju apņēmies jūs apmeklēt, lai iegūtu kādu augli arī starp jums tāpat kā starp pārējām tautām, (bet līdz šim tiku aizkavēts).
16በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና።
14Grieķiem un barbariem, mācītiem un nemācītiem es esmu parādnieks.
17ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና።
15Tāpēc (kas attiecas uz mani) es esmu gatavs sludināt evaņģēliju arī jums, kas esat Romā.
18እውነትን በዓመፃ በሚከለክሉ ሰዎች በኃጢአተኝነታቸውና በዓመፃቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቍጣ ከሰማይ ይገለጣልና፤
16Es nekaunos evaņģēlija, jo tas ir Dieva spēks katra ticīgā pestīšanai, vispirms jūda, tad grieķa.
19እግዚአብሔር ስለ ገለጠላቸው፥ ስለ እግዚአብሔር ሊታወቅ የሚቻለው በእነርሱ ዘንድ ግልጥ ነውና።
17Jo tanī atklājas Dieva taisnība no ticības uz ticību, kā rakstīts: Taisnīgais dzīvo no ticības. (Hab.2,4)
20የማይታየው ባሕርይ እርሱም የዘላለም ኃይሉ ደግሞም አምላክነቱ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ ከተሠሩት ታውቆ ግልጥ ሆኖ ይታያልና፤ ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ፤ ነገር ግን በአሳባቸው ከንቱ ሆኑ የማያስተውለውም ልባቸው ጨለመ።
18Jo Dieva dusmas parādās no debesīm pār katru to cilvēku bezdievību un netaisnību, kas Dieva patiesību nomāc netaisnībā,
22ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ፥
19Jo kas par Dievu zināms, tas viņiem pasludināts, jo Dievs viņiem to ir atklājis.
23የማይጠፋውንም የእግዚአብሔር ክብር በሚጠፋ ሰውና በወፎች አራት እግር ባላቸውም በሚንቀሳቀሱትም መልክ መስለው ለወጡ።
20Jo tas, kas Viņā neredzams, un Viņa mūžīgais spēks, un dievība no pasaules radīšanas ir ar prātu saskatāmi Viņa darbos; tāpēc viņi ir neattaisnojami.
24ስለዚህ እርስ በርሳቸው ሥጋቸውን ሊያዋርዱ እግዚአብሔር በልባቸው ፍትወት ወደ ርኵስነት አሳልፎ ሰጣቸው፤
21Jo tie, pazinuši Dievu, negodināja Viņu kā Dievu un nebija Viņam pateicīgi, bet savās domās kļuva tukši, un viņu neprātīgā sirds tika aptumšota;
25ይህም የእግዚአብሔርን እውነት በውሸት ስለ ለወጡ በፈጣሪም ፈንታ የተፈጠረውን ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው፤ እርሱም ለዘላለም የተባረከ ነው፤ አሜን።
22Apgalvodami, ka viņi ir gudri, tie kļuva nelgas;
26ስለዚህ እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤
23Un nemirstīgā Dieva godību tie apmainīja pret iznīcīgajiem cilvēkiem un putniem, un četrkājaiņiem, un rāpuļiem līdzīgiem tēliem.
27እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ።
24Tāpēc Dievs viņus atstājis viņu siržu kārībām un nešķīstībai, lai tie paši apgānītu savas miesas.
28እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው፤
25Dieva patiesību tie apmainīja pret meliem un pielūdza, un kalpoja drīzāk radībai nekā Radītājam, kas lai augsti teikts mūžīgi mūžos. Amen.
29ዓመፃ ሁሉ፥ ግፍ፥ መመኘት፥ ክፋት ሞላባቸው፤ ቅናትን፥ ነፍስ መግደልን፥ ክርክርን፥ ተንኰልን፥ ክፉ ጠባይን ተሞሉ፤ የሚያሾከሹኩ፥
26Tāpēc Dievs tos atstājis kauna pilnām kārībām, jo viņu sievietes dabisko kopdzīvi apmainījušas pret pretdabisko.
30ሐሜተኞች፥ አምላክን የሚጠሉ፥ የሚያንገላቱ፥ ትዕቢተኞች፥ ትምክህተኞች፥ ክፋትን የሚፈላለጉ፥ ለወላጆቻቸው የማይታዘዙ፥
27Tāpat arī vīrieši, atstādami dabisko kopdzīvi ar sievietēm, iedegās kaislībās viens pret otru, piekopdami netiklību vīrietis ar vīrieti un saņemdami nopelnīto sodu par saviem maldiem paši pie sevis.
31የማያስተውሉ፥ ውል የሚያፈርሱ፥ ፍቅር የሌላቸው፥ ምሕረት ያጡ ናቸው፤
28Un tāpēc, ka viņi neuzskatīja Dieva atzīšanu par vajadzīgu, Dievs tos atstāja izvirtušām tieksmēm, lai tie darītu to, kas neklājas.
32እንደነዚህ ለሚያደርጉት ሞት ይገባቸዋል የሚለውን የእግዚአብሔርን ሕግ እያወቁ እነዚህን ከሚያደርጉ ጋር ይስማማሉ እንጂ አድራጊዎች ብቻ አይደሉም።
29Viņi ir visādām netaisnībām, ļaunprātībām, netiklībām, mantkārībām, ļaunumiem pārpildīti; viņi ir pilni skaudības, slepkavību, ķildu, viltības, nedarbu, mēlnesības;
30Viņi ir neslavas cēlāji, Dieva nīdēji, ķengātāji, augstprātīgi, lielīgi, ļaunumu izgudrotāji, nepaklausīgi vecākiem,
31Neprātīgi, nesaticīgi, cietsirdīgi, neuzticīgi, nežēlīgi.
32Lai gan viņi Dieva taisnību pazina, tie nenojauta, ka tie, kas tā dara, ir pelnījuši nāvi; un ne tikai tie, kas tā dara, bet arī tie, kas darītājiem piekrīt.