Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Romans

2

1Tāpēc neviens cilvēks, kas tiesā, nepaliek bez vainas, jo, citu tiesādams, tu notiesā pats sevi, jo tu dari to, ko tu nosodi.
1ስለዚህ፥ አንተ የምትፈርድ ሰው ሁሉ ሆይ፥ የምታመካኘው የለህም፤ በሌላው በምትፈርድበት ነገር ራስህን ትኰንናለህና፤ አንተው ፈራጁ እነዚያን ታደርጋለህና።
2Mēs zinām, ka Dievs spriež taisnīgu tiesu tiem, kas tā dara.
2እንደዚህም በሚያደርጉት ላይ የእግዚአብሔር ፍርድ እውነተኛ እንደ ሆነ እናውቃለን።
3Bet vai tu, cilvēk, kas tiesā tos, kas tā dara, bet pats dari to pašu, domā, ka tu izbēgsi Dieva tiesai?
3አንተም እንደዚህ በሚያደርጉ የምትፈርድ ያንም የምታደርግ ሰው ሆይ፥ አንተ ከእግዚአብሔር ፍርድ የምታመልጥ ይመስልሃልን?
4Vai tu nicini Viņa labuma un pacietības, un lēnprātības bagātību, neapzinādamies, ka Dieva labvēlība ved tevi pie atgriešanās?
4ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሐ እንዲመራህ ሳታውቅ የቸርነቱንና የመቻሉን የትዕግሥቱንም ባለጠግነት ትንቃለህን?
5Bet tavas stūrgalvības un negandarītājas sirds dēļ tu krāj dusmas Dieva dusmu un taisnīgās tiesas parādīšanās dienai.
5ነገር ግን እንደ ጥንካሬህና ንስሐ እንደማይገባ ልብህ የእግዚአብሔር ቅን ፍርድ በሚገለጥበት በቍጣ ቀን ቍጣን በራስህ ላይ ታከማቻለህ።
6Viņš katram atlīdzinās saskaņā ar tā darbiem:
6እርሱ ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ያስረክበዋል፤
7Tiem, kas, pacietībā labus darbus darīdami, meklē svētlaimību un godu, un neiznīcību, - ar mūžīgo dzīvi,
7በበጎ ሥራ በመጽናት ምስጋናንና ክብርን የማይጠፋንም ሕይወት ለሚፈልጉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል፤
8Bet tiem, kas pretojas un nemeklē patiesību, bet nododas netaisnībai, - ar dusmām un bardzību.
8ለዓመፃ በሚታዘዙ እንጂ ለእውነት በማይታዘዙትና በአድመኞች ላይ ግን ቍጣና መቅሠፍት ይሆንባቸዋል።
9Bēdas un apspiešana ikvienai cilvēka dvēselei, kas dara ļaunu, vispirms jūdam un arī grieķim.
9ክፉውን በሚያደርግ ሰው ነፍስ ሁሉ መከራና ጭንቀት ይሆንበታል፥ አስቀድሞ በአይሁዳዊ ደግሞም በግሪክ ሰው፤
10Bet svētlaimība un gods, un miers ikvienam, kas dara labu, vispirms jūdam un arī grieķim,
10ነገር ግን በጎ ሥራ ለሚያደርጉ ሁሉ ምስጋናና ክብር ሰላምም ይሆንላቸዋል፥ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው።
11Jo Dievs neuzlūko cilvēka personu.
11እግዚአብሔር ለሰው ፊት አያዳላምና።
12Jo tie, kam nebija likuma un ir grēkojuši, bez likuma ies pazušanā; bet tie, kam bija likums un ir grēkojuši, pēc likuma tiks tiesāti.
12ያለ ሕግ ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ ያለ ሕግ ደግሞ ይጠፋሉና፤ ሕግም ሳላቸው ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ በሕግ ይፈረድባቸዋል፤
13Jo ne likuma dzirdētāji ir taisnīgi Dieva priekšā, bet gan likuma izpildītāji būs taisnīgi.
13በእግዚአብሔር ፊት ሕግን የሚያደርጉት ይጸድቃሉ እንጂ ሕግን የሚሰሙ ጻድቃን አይደሉምና።
14Jo ja pagāni, kam likuma nav, dabiski izpilda to, ko likums prasa, tad viņi paši ir sev likums, lai gan viņiem tāda likuma nav.
14ሕግ የሌላቸው አሕዛብ ከባሕርያቸው የሕግን ትእዛዝ ሲያደርጉ፥ እነዚያ ሕግ ባይኖራቸው እንኳ ለራሳቸው ሕግ ናቸውና፤
15Viņi rāda darbos, ka likums ierakstīts viņu sirdīs; viņu sirdsapziņa ir viņu lieciniece, un to domas viena otru vai nu apsūdzēs, vai arī aizstāvēs
15እነርሱም ሕሊናቸው ሲመሰክርላቸው፥ አሳባቸውም እርስ በርሳቸው ሲካሰስ ወይም ሲያመካኝ በልባቸው የተጻፈውን የሕግ ሥራ ያሳያሉ።
16Tanī dienā, kad Dievs tiesās cilvēku noslēpumus saskaņā ar manu evaņģēliju caur Jēzu Kristu.
16ይህም እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ እኔ በወንጌል እንዳስተማርሁ በሰው ዘንድ የተሰወረውን በሚፈርድበት ቀን ይሆናል።
17Bet ja tu saucies jūds un paļaujies uz likumu, un lepojies, ka tev ir Dievs,
17አንተ ግን አይሁዳዊ ብትባል በሕግም ብትደገፍ በእግዚአብሔርም ብትመካ፥
18Un tu pazīsti Viņa prātu un, likuma pamācīts, tu atzīsti labāko,
18ፈቃዱንም ብታውቅ ከሕግም ተምረህ የሚሻለውን ፈትነህ ብትወድ፤
19Tu apzinies, ka tu esi aklo vadonis, gaisma tiem, kas ir tumsībā,
19በሕግም የእውቀትና የእውነት መልክ ስላለህ፥ የዕውሮች መሪ፥ በጨለማም ላሉ ብርሃን፥ የሰነፎችም አስተማሪ፥ የሕፃናትም መምህር እንደ ሆንህ በራስህ ብትታመን፤
20Nesaprātīgo audzinātājs, nepieaugušo skolotājs, kam likumā dota zināšanas un patiesības būtība,
21እንግዲህ አንተ ሌላውን የምታስተምር ራስህን አታስተምርምን? አትስረቅ ብለህ የምትሰብክ ትሰርቃለህን?
21Kā tad tu citu māci, bet pats sevi nemāci? Tu sludini, ka nebūs zagt, bet tu zodz;
22አታመንዝር የምትል ታመነዝራለህን? ጣዖትን የምትጸየፍ ቤተ መቅደስን ትዘርፋለህን?
22Tu saki, ka nebūs laulību pārkāpt, bet pats pārkāp; tu nicini elkus, bet piekop svētzādzību;
23በሕግ የምትመካ ሕግን በመተላለፍ እግዚአብሔርን ታሳፍራለህን?
23Tu lepojies ar likumu, bet, pārkāpdams to, tu pulgo Dievu?
24በእናንተ ሰበብ የእግዚአብሔር ስም በአሕዛብ መካከል ይሰደባልና ተብሎ እንደ ተጻፈ።
24(Jo, kā rakstīts, jūsu dēļ Dieva vārds starp pagāniem tiek zaimots.) (Is.52,5)
25ሕግን ብታደርግ መገረዝስ ይጠቅማል፤ ሕግን ተላላፊ ብትሆን ግን መገረዝህ አለ መገረዝ ሆኖአል።
25Apgraizīšanai ir nozīme, ja tu izpildi likumu, bet ja tu esi likuma pārkāpējs, tad tava apgraizīšana ir kļuvusi neapgraizīšana.
26እንግዲህ ያልተገረዘ ሰው የሕግን ሥርዓት ቢጠብቅ አለመገረዙ እንደ መገረዝ ሆኖ አይቈጠርለትምን?
26Bet ja neapgraizītais izpildītu likuma prasības, vai tad viņa neapgraizīšana neskaitīsies apgraizīšana?
27ከፍጥረቱም ያልተገረዘ ሕግን የሚፈጽም ሰው የሕግ መጽሐፍና መገረዝ ሳለህ ሕግን በምትተላለፈው በአንተ ይፈርድብሃል።
27Un vai tas, kas miesīgi neapgraizīts, bet izpilda likumu, netiesās tevi, kam ir Raksti un apgraizīšana, bet esi likuma pārkāpējs?
28በግልጥ አይሁዳዊ የሆነ አይሁዳዊ አይደለምና፥ በግልጥ በሥጋ የሚደረግ መገረዝም መገረዝ አይደለምና፤
28Jo ne tas ir jūds, kas ārīgi ir tāds, un ne tā ir apgraizīšana, kas ir ārīgi pie miesas,
29ዳሩ ግን በስውር አይሁዳዊ የሆነ አይሁዳዊ ነው፥ መገረዝም በመንፈስ የሚደረግ የልብ መገረዝ ነው እንጂ በመጽሐፍ አይደለም፤ የእርሱ ምስጋና ከእግዚአብሔር ነው እንጂ ከሰው አይደለም።
29Bet jūds ir tas, kas tāds ir slepenībā, un sirds apgraizīšana ir garā, bet ne burtā; tādam gods ir nevis no cilvēkiem, bet no Dieva.