1Vai jūs, brāļi, nezināt (jo es runāju tiem, kas zina likumu), ka likums valda pār cilvēku tik ilgi, kamēr viņš dzīvo?
1ወንድሞች ሆይ፥ ሕግን ለሚያውቁ እናገራለሁና ሰው ባለበት ዘመን ሁሉ ሕግ እንዲገዛው አታውቁምን?
2Tā - precēta sieva ir saistīta ar likumu, kamēr vīrs dzīvs, bet ja viņas vīrs miris, tad viņa ir brīva no likuma, kas saistīja ar vīru.
2ያገባች ሴት ባልዋ በሕይወት ሲኖር ከእርሱ ጋር በሕግ ታስራለችና፤ ባልዋ ቢሞት ግን ስለ ባል ከሆነው ሕግ ተፈትታለች።
3Tāpēc, kamēr vīrs dzīvs, tā sauksies laulības pārkāpēja, ja biedrosies ar citu vīru; bet pēc viņas vīra nāves tā ir brīva no likuma saistībām ar vīru, un viņa nebūs laulības pārkāpēja, ja tā dzīvos ar citu vīru.
3ስለዚህ ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች፤ ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ አይደለችም።
4Tātad, mani brāļi, Kristus miesa arī jūs ir nomērdējusi likumam, lai jūs piederētu Citam, Tam, kas no miroņiem uzcēlies, lai mēs nestu augļus Dievam.
4እንዲሁ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ ደግሞ በክርስቶስ ሥጋ ለሕግ ተገድላችኋል፤ ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ፥ እናንተ ለሌላው፥ ከሙታን ለተነሣው፥ ለእርሱ ትሆኑ ዘንድ።
5Jo kamēr mēs dzīvojām miesā, likuma atklātās grēcīgās kaislības darbojās mūsu locekļos, lai mēs nestu augļus nāvei.
5በሥጋ ሳለን በሕግ የሚሆን የኃጢአት መሻት ለሞት ፍሬ ሊያፈራ በብልቶቻችን ይሠራ ነበርና፤
6Bet tagad mēs esam atbrīvoti no nāves likuma, kurā tikām turēti, lai kalpotu jaunā garā, bet ne novecojušam burtam.
6አሁን ግን ለእርሱ ለታሰርንበት ስለ ሞትን፥ ከሕግ ተፈትተናል፥ ስለዚህም በአዲሱ በመንፈስ ኑሮ እንገዛለን እንጂ በአሮጌው በፊደል ኑሮ አይደለም።
7Ko tad lai sakām? Vai likums ir grēks? Nekādā ziņā! Bet es grēka nepazītu, ja nebūtu likuma, jo es nezinātu, kas ir iekāre, ja likums nesacītu: Tev nebūs iekārot!
7እንግዲህ ምን እንላለን? ሕግ ኃጢአት ነውን? አይደለም፤ ነገር ግን በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ። አትመኝ ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና።
8Bet grēks, izmantojot izdevību, caur likumu, modināja manī visas iekāres; jo bez likuma grēks būtu miris;
8ኃጢአት ግን ምክንያት አግኝቶ ምኞትን ሁሉ በትእዛዝ ሠራብኝ፤ ኃጢአት ያለ ሕግ ምውት ነውና።
9Es gan kādreiz dzīvoju bez likuma, bet, kad nāca likums, grēks atdzīvojās;
9እኔም ዱሮ ያለ ሕግ ሕያው ነበርሁ፤ ትእዛዝ በመጣች ጊዜ ግን ኃጢአት ሕያው ሆነ እኔም ሞትሁ፤
10Turpretī es nomiru. Tā izrādījās, ka likums, kas bija domāts dzīvei, man atnesa nāvi.
10ለሕይወትም የተሰጠችውን ትእዛዝ እርስዋን ለሞት ሆና አገኘኋት፤
11Jo grēks, izmantojot izdevību, caur likumu mani pievīla un tā nonāvēja mani.
11ኃጢአት ምክንያት አግኝቶ በትእዛዝ አታሎኛልና በእርስዋም ገድሎኛል።
12Likums gan ir svēts, un bauslība ir svēta un taisnīga, un laba.
12ስለዚህ ሕጉ ቅዱስ ነው ትእዛዚቱም ቅድስትና ጻድቅት በጎም ናት።
13Vai tad tas, kas labs, man atnesis nāvi? Nekādā ziņā! Bet grēks, lai parādītos kā grēks, izmantodams labo, man atnesa nāvi, lai grēks, pateicoties likumam, kļūtu pār mēru grēcīgs.
13እንግዲህ በጎ የሆነው ነገር ለእኔ ሞት ሆነብኝን? አይደለም፥ ነገር ግን ኃጢአት ሆነ፤ ኃጢአትም በትእዛዝ ምክንያት ያለ ልክ ኃጢአተኛ ይሆን ዘንድ፥ ኃጢአትም እንዲሆን ይገለጥ ዘንድ በጎ በሆነው ነገር ለእኔ ሞትን ይሠራ ነበር።
14Jo mēs zinām, ka likums ir garīgs, bet es, grēkam pārdots, esmu miesīgs.
14ሕግ መንፈሳዊ እንደ ሆነ እናውቃለንና፤ እኔ ግን ከኃጢአት በታች ልሆን የተሸጥሁ የሥጋ ነኝ።
15Es nesaprotu, ko daru: jo es nedaru labu, ko gribu, bet es daru ļaunu, ko ienīstu.
15የማደርገውን አላውቅምና፤ የምጠላውን ያን አደርጋለሁና ዳሩ ግን የምወደውን እርሱን አላደርገውም።
16Bet ja es daru to, ko negribu, tad es piekrītu likumam, ka tas ir labs.
16የማልወደውን ግን የማደርግ ከሆንሁ ሕግ መልካም እንደ ሆነ እመሰክራለሁ።
17Bet tagad jau ne es to daru, bet grēks, kas manī mājo.
17እንደዚህ ከሆነ ያን የማደርገው አሁን እኔ አይደለሁም፥ በእኔ የሚያድር ኃጢአት ነው እንጂ።
18Jo es zinu, ka labais manī, tas ir, manā miesā, nemājo. Man ir tieksme labu gribēt, bet labā izpildīšanu es sevī neatrodu.
18በእኔ ማለት በሥጋዬ በጎ ነገር እንዳይኖር አውቃለሁና፤ ፈቃድ አለኝና፥ መልካሙን ግን ማድረግ የለኝም።
19Jo es nedaru labo, ko vēlos, bet daru ļauno, ko nevēlos.
19የማልወደውን ክፉን ነገር አደርጋለሁና ዳሩ ግን የምወደውን በጎውን ነገር አላደርገውም።
20Bet ja es daru to, ko nevēlos, tad jau ne es to daru, bet grēks, kas manī mājo.
20የማልወደውን የማደርግ ከሆንሁ ግን ያን የማደርገው አሁን እኔ አይደለሁም፥ በእኔ የሚኖር ኃጢአት ነው እንጂ።
21Tātad es atrodu likumu, kas tad, kad gribu labu darīt, tuvojas man ar ļaunu:
21እንግዲያስ መልካሙን አደርግ ዘንድ ስወድ በእኔ ክፉ እንዲያድርብኝ ሕግን አገኛለሁ።
22Jo iekšējais cilvēks priecājas par Dieva likumu,
22በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛልና፥
23Bet citu likumu es redzu savos locekļos. Tas karo pret mana prāta likumu un pakļauj mani grēka likumam, kas ir manos locekļos.
23ነገር ግን በብልቶቼ ከአእምሮዬ ሕግ ጋር የሚዋጋውንና በብልቶቼ ባለ በኃጢአት ሕግ የሚማርከኝን ሌላ ሕግ አያለሁ።
24Es, nelaimīgais cilvēks! Kas mani atbrīvos no šīs nāvi nesējas miesas?
24እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ! ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?
25Dieva žēlastība caur mūsu Kungu Jēzu Kristu! Tātad ar prātu es kalpoju Dieva likumam, bet ar miesu - grēka likumam.
25በኢየሱስ ክርስቶስ በጌታችን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። እንግዲያስ እኔ በአእምሮዬ ለእግዚአብሔር ሕግ፥ በሥጋዬ ግን ለኃጢአት ሕግ እገዛለሁ።