1Broliai, aiškinu jums Evangeliją, kurią jums paskelbiau, kurią jūs ir priėmėte ir kurioje stovite,
1ወንድሞች ሆይ፥ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለሁ፤
2ir kuria esate išgelbėti,jeigu jūs laikotės to žodžio, kurį jums paskelbiau; kitaip jūs įtikėjote veltui.
2በከንቱ ካላመናችሁ በቀር፥ ብታስቡት፥ በምን ቃል እንደ ሰበክሁላችሁ አሳስባችኋለሁ።
3Pirmiausia jums perdaviau tai, ką pats gavau: kad Kristus numirė už mūsų nuodėmes pagal Raštus;
3እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ። መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥
4ir kad Jis buvo palaidotas, ir kad prisikėlė trečią dieną pagal Raštus;
4መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥
5ir kad Jis pasirodė Kefui, po to dvylikai.
5ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤
6Po to Jis pasirodė iš karto daugiau nei penkiems šimtams brolių, kurių daugumas tebegyvena iki šiol, o kai kurie yra užmigę.
6ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤
7Po to Jis pasirodė Jokūbui, paskui visiems apaštalams.
7ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤
8O visų paskiausiai, lyg ne laiku gimusiam, Jis pasirodė ir man.
8ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ።
9Juk aš esu mažiausias iš apaštalų, nevertas vadintis apaštalu, nes persekiojau Dievo bažnyčią.
9እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ፤
10Bet Dievo malone esu, kas esu, ir Jo malonė man neliko bergždžia, bet aš darbavausi daug daugiau už juos visus, nors ne aš, bet Dievo malonė, esanti su manimi.
10ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።
11Taigi ar aš, ar jie,taip mes skelbiame, ir taip jūs įtikėjote.
11እንግዲህስ እኔ ብሆን እነርሱም ቢሆኑ እንዲሁ እንሰብካለን እንዲሁም አመናችሁ።
12Jeigu apie Kristų skelbiama, kad Jis buvo prikeltas iš numirusių, tad kaip kai kurie iš jūsų sako, kad nėra mirusiųjų prisikėlimo?!
12ክርስቶስ ከሙታን እንደ ተነሣ የሚሰበክ ከሆነ ግን ከእናንተ አንዳንዶቹ። ትንሣኤ ሙታን የለም እንዴት ይላሉ?
13Jeigu nėra mirusiųjų prisikėlimo, tai Kristus nebuvo prikeltas.
13ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሣማ፤
14O jei Kristus nebuvo prikeltas, tai tuščias mūsų skelbimas ir tuščias jūsų tikėjimas.
14ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት፤
15Ir mes tada liekame melagingi Dievo liudytojai, nes liudijome apie Dievą, kad Jis prikėlė Kristų, kurio Jis nėra prikėlęs, jeigu mirusieji neprisikelia.
15ደግሞም። ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን በእግዚአብሔር ላይ ስለ መሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም።
16Nes jei mirusieji neprisikelia, tada ir Kristus nebuvo prikeltas.
16ሙታን የማይነሡ ከሆነ ክርስቶስ አልተነሣማ፤
17O jei Kristus nebuvo prikeltas, tai jūsų tikėjimas tuščias; jūs dar tebesate savo nuodėmėse.
17ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ።
18Tuomet ir užmigusieji Kristuje yra žuvę.
18እንግዲያስ በክርስቶስ ያንቀላፉት ደግሞ ጠፍተዋላ።
19Ir jei vien tik šiame gyvenime mes viliamės Kristumi, tai mes esame labiausiai apgailėtini iš visų žmonių.
19በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።
20Bet dabar Kristus yra prikeltas iš numirusiųpirmasis iš užmigusiųjų.
20አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።
21Kaip per žmogųmirtis, taip per žmogų ir mirusiųjų prisikėlimas.
21ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።
22Kaip Adome visi miršta, taip Kristuje visi bus atgaivinti,
22ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።
23tačiau kiekvienas pagal savo eilę: Kristuspirmasis, vėliaupriklausantys Kristui Jo atėjimo metu.
23ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ተራ ይሆናል፤ ክርስቶስ እንደ በኩራት ነው፥ በኋላም በመምጣቱ ለክርስቶስ የሆኑት ናቸው፤
24Po to bus galas, kai Jis perduos karalystę Dievui Tėvui, sunaikinęs visas kunigaikštystes, visas valdžias ir jėgas.
24በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል።
25Nes Jis turi valdyti, kol paguldys visus priešus po savo kojomis.
25ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሩ በታች እስኪያደርግ ድረስ ሊነግሥ ይገባዋልና።
26Kaip paskutinis priešas bus sunaikinta mirtis.
26የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው፤
27Nes “Jis visa paklojo Jam po kojų”. Bet kai Jis sako, kad visa paklota, tai savaime suprantama, kad išskyrus Tą, kuris Jam visa paklojo.
27ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን። ሁሉ ተገዝቶአል ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው።
28Kai Jam bus visa pajungta, tada ir pats Sūnus nusilenks Tam, kuris viską Jam pajungė, kad Dievas būtų viskas visame kame.
28ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል።
29Kita vertus, ką darys tie, kuriuos krikštija už mirusiuosius? Jei iš viso mirusieji neprisikels, tai kam gi jie krikštijami už mirusiuosius?
29እንዲያማ ካልሆነ፥ ስለ ሙታን የሚጠመቁ ምን ያደርጋሉ? ሙታንስ ከቶ የማይነሡ ከሆነ፥ ስለ እነርሱ የሚጠመቁ ስለ ምንድር ነው?
30Ir kodėl ir mes kas valandą esame pavojuje?
30እኛስ ዘወትር በሚያስፈራ ኑሮ የምንኖር ስለ ምንድር ነው?
31Prisiekiu savo pasididžiavimu jumis, broliai, mūsų Viešpatyje Jėzuje Kristuje, jog aš kasdien mirštu!
31በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ባለኝ በእናንተ ትምክህት እየማልሁ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕለት ዕለት እሞታለሁ።
32Jei grynai kaip žmogus kovojau Efeze su laukiniais žvėrimis, tai kokia man iš to nauda? Jeigu mirusieji neprisikels, tai “valgykime ir gerkime, nes rytoj mirsime”.
32እንደ ሰው በኤፌሶን ከአውሬ ጋር ከታገልሁ፥ ሙታንስ የማይነሡ ከሆነ፥ ምን ይጠቅመኛል? ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ።
33Neapsirikite: “Blogos draugijos gadina gerus papročius!”
33አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።
34Pabuskite teisumui ir nenuodėmiaukite, nes kai kurie iš jūsų nepažįsta Dievo. Tai sakau jūsų gėdai.
34በጽድቅ ንቁ ኃጢአትንም አትሥሩ፤ እግዚአብሔርን የማያውቁ አሉና፤ አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ።
35Bet gal kas paklaus: “Kaip bus prikelti mirusieji? Su kokiu kūnu jie pasirodys?”
35ነገር ግን ሰው። ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።
36Kvaily! Ką tu pasėji, neatgyja, jei prieš tai nenumiršta.
36አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም፤
37Ir ką besėtum, tu sėji ne būsimąjį kūną, bet pliką grūdą, sakysime, kviečių ar kitokių javų.
37የምትዘራውም፥ ስንዴ ቢሆን ከሌላም ዓይነት የአንዱ ቢሆን፥ ቅንጣት ብቻ ነው እንጂ የምትዘራው የሚሆነውን አካል አይደለም፤
38Tuo tarpu Dievas duoda jam kūną tokį, koks Jam patinka, ir kiekvienai sėklai jos kūną.
38እግዚአብሔር ግን እንደ ወደደ አካልን ይሰጠዋል ከዘሮችም ለእያንዳንዱ የገዛ አካሉን ይሰጠዋል።
39Ne visi kūnai yra vienodi. Vienoks žmonių kūnas, kitoks gyvulių, kitoks žuvų ir kitoks paukščių.
39ሥጋ ሁሉ አንድ አይደለም፥ የሰው ሥጋ ግን አንድ ነው፥ የእንስሳም ሥጋ ሌላ ነው፥ የወፎችም ሥጋ ሌላ ነው፥ የዓሣም ሥጋ ሌላ ነው።
40Taip pat yra dangaus kūnai ir žemės kūnai, bet vienokia dangaus kūnų šlovė ir kitokia žemės kūnų.
40ደግሞ ሰማያዊ አካል አለ፥ ምድራዊም አካል አለ፤ ነገር ግን የሰማያዊ አካል ክብር ልዩ ነው፥ የምድራዊም አካል ክብር ልዩ ነው።
41Vienokia yra saulės šlovė, kitokia šlovė mėnulio ir dar kitokia šlovė žvaigždžių. Ir žvaigždė nuo žvaigždės skiriasi šlove.
41የፀሐይ ክብር አንድ ነው የጨረቃም ክብር ሌላ ነው የከዋክብትም ክብር ሌላ ነው፤ በክብር አንዱ ኮከብ ከሌላው ኮከብ ይለያልና።
42Taip ir su mirusiųjų prisikėlimu. Sėjamas gendantis kūnas, prikeliamas negendantis.
42የሙታን ትንሣኤ ደግሞ እንዲሁ ነው። በመበስበስ ይዘራል፥ ባለመበስበስ ይነሣል፤
43Sėjamas negarbingas, prikeliamas šlovingas. Sėjamas silpnas, prikeliamas galingas.
43በውርደት ይዘራል፥ በክብር ይነሣል፤ በድካም ይዘራል፥ በኃይል ይነሣል፤
44Sėjamas sielinis kūnas, prikeliamas dvasinis kūnas. Yra sielinis kūnas ir yra dvasinis kūnas.
44ፍጥረታዊ አካል ይዘራል፥ መንፈሳዊ አካል ይነሣል። ፍጥረታዊ አካል ካለ መንፈሳዊ አካል ደግሞ አለ።
45Taip ir parašyta: “Pirmasis žmogus Adomas tapo gyva siela”; paskutinysis Adomasgyvybę teikiančia dvasia.
45እንዲሁ ደግሞ። ፊተኛው ሰው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ ተብሎ ተጽፎአል፤ ኋለኛው አዳም ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ።
46Bet ne dvasinis pirmiau, o sielinis, ir tik po to dvasinis.
46ነገር ግን አስቀድሞ ፍጥረታዊው ቀጥሎም መንፈሳዊው ነው እንጂ መንፈሳዊው መጀመሪያ አይደለም።
47Pirmasis žmogusiš žemės, žemiškas; antrasis žmogusViešpats iš dangaus.
47የፊተኛው ሰው ከመሬት መሬታዊ ነው፤ ሁለተኛው ሰው ከሰማይ ነው።
48Koks buvo žemiškasis, tokie yra ir žemiškieji, o koks yra dangiškasis, tokie yra ir dangiškieji.
48መሬታዊው እንደ ሆነ መሬታውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው፥ ሰማያዊው እንደ ሆነ ሰማያውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው።
49Ir kaip nešiojame žemiškojo atvaizdą, taip nešiosime ir dangiškojo atvaizdą.
49የዚያንም የመሬታዊውን መልክ እንደ ለበስን የሰማያዊውን መልክ ደግሞ እንለብሳለን።
50Bet aš jums, broliai, sakau, kad kūnas ir kraujas nepaveldės Dievo karalystės, ir kas genda, nepaveldės to, kas negenda.
50ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ። ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም።
51Aš jums atskleidžiu paslaptį: ne visi užmigsime, bet visi būsime pakeisti,
51እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበት ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።
52staiga, viena akimirka, skambant paskutiniam trimitui. Trimitas nuskambės, ir mirusieji bus prikelti negendantys, o mes būsime pakeisti.
53ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና።
53Nes šis gendantis turi apsivilkti negendamybe, ir šis marus apsivilkti nemarybe.
54ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ። ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።
54Kada šis gendantis apsivilks negendamybe ir šis marusis apsivilks nemarybe, tada išsipildys užrašytas žodis: “Pergalė prarijo mirtį!
55ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ?
55Kurgi, mirtie, tavo geluonis? Kurgi, mirtie, tavo pergalė?”
56የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤
56Mirties geluonis yra nuodėmė, o nuodėmės jėgaįstatymas.
57ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።
57Bet dėkui Dievui, kuris duoda mums pergalę per mūsų Viešpatį Jėzų Kristų!
58ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።
58Todėl, mano mylimieji broliai, būkite tvirti, nepajudinami, visada gausūs Viešpaties darbais, žinodami, kad jūsų triūsas ne veltui Viešpatyje.