Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Corinthians

14

1Siekite meilės ir trokškite dvasinių dovanų, ypač, kad pranašautumėte.
1ፍቅርን ተከታተሉ፥ መንፈሳዊ ስጦታንም ይልቁንም ትንቢት መናገርን በብርቱ ፈልጉ።
2Kas kalba kalbomis, ne žmonėms kalba, bet Dievui; niekas jo nesupranta, nes jis dvasioje kalba paslaptis.
2በልሳን የሚናገርስ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርም፤ የሚያስተውለው የለምና፥ በመንፈስ ግን ምሥጢርን ይናገራል፤
3Bet kas pranašauja, tas kalba žmonių ugdymui, paraginimui ir paguodai.
3ትንቢትን የሚናገር ግን ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ለሰው ይናገራል።
4Kas kalba kalbomis, pats save ugdo, o kas pranašauja­ugdo bažnyčią.
4በልሳን የሚናገር ራሱን ያንጻል፤ ትንቢትን የሚናገር ግን ማኅበሩን ያንጻል።
5Aš norėčiau, kad jūs visi kalbėtumėte kalbomis, bet būtų geriau, jei pranašautumėte, nes kas pranašauja, yra didesnis už tą, kuris kalba kalbomis, nebent pastarasis ir aiškintų, kad būtų ugdoma bažnyčia.
5ሁላችሁ በልሳኖች ልትናገሩ እወድ ነበር፥ ትንቢትን ልትናገሩ ግን ከዚህ ይልቅ እወዳለሁ፤ ማኅበሩ ይታነጽ ዘንድ ንግግሩን ባይተረጐም በልሳኖች ከሚናገር ትንቢትን የሚናገር ይበልጣል።
6Bet dabar, broliai, jei ateičiau pas jus, kalbėdamas kalbomis, kokia jums būtų nauda, jeigu neskelbčiau jums apreiškimo, pažinimo, pranašystės ar mokymo?
6አሁን ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ወደ እናንተ መጥቼ በልሳኖች ብናገር፥ በመግለጥ ወይም በእውቀት ወይም በትንቢት ወይም በትምህርት ካልነገርኋችሁ ምን እጠቅማችኋለሁ?
7Taip pat ir negyvi daiktai, skleidžiantys garsus, ar tai būtų fleita, ar kanklės, jei neduotų skirtingų garsų, iš ko pažintume, kas grojama ar skambinama?
7ነፍስ የሌለበት ነገር እንኳ ዋሽንትም ክራርም ቢሆን ድምፅ ሲሰጥ የድምፁን ልዩነት ባይገልጥ በዋሽንት የሚነፋው ወይስ በክራር የሚመታው መዝሙር እንዴት ይታወቃል?
8Ir jeigu trimitas duotų neaiškų garsą, kas ruoštųsi į mūšį?
8ደግሞም መለከት የማይገለጥን ድምፅ ቢሰጥ ለጦርነት ማን ይዘጋጃል?
9Tas pat ir su jumis. Jei kalbėsite nesuprantamus žodžius, kaip bus galima suprasti, ką sakote? Jūs kalbėsite vėjams!
9እንዲሁ እናንተ ደግሞ የተገለጠውን ቃል በአንደበት ባትናገሩ ሰዎች የምትናገሩትን እንዴት አድርገው ያስተውሉታል? ለነፋስ የምትናገሩ ትሆናላችሁና።
10Kas žino, kiek daug yra įvairių kalbų pasaulyje, bet nė viena iš jų nėra bereikšmė.
10በዓለም ምናልባት ቁጥር የሌለው የቋንቋ ዓይነት ይኖራል ቋንቋም የሌለው ሕዝብ የለም፤
11Todėl jei nesuprantu kalbos prasmės, būsiu kalbėtojui svetimšalis, ir kalbėtojas bus man svetimšalis.
11እንግዲህ የቋንቋውን ፍች ባላውቅ ለሚናገረው እንግዳ እሆናለሁ፥ የሚናገረውም ለእኔ እንግዳ ይሆናል።
12Taigi ir jūs, karštai trokštantys dvasinių dovanų, siekite jų bažnyčios ugdymui, kad gausiai jų turėtumėte.
12እንዲሁ ደግሞ እናንተ መንፈሳዊ ስጦታን በብርቱ የምትፈልጉ ከሆናችሁ ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ እንዲበዛላችሁ ፈልጉ።
13Todėl, kas kalba kalbomis, tesimeldžia, kad galėtų aiškinti.
13ስለዚህ በልሳን የሚናገር እንዲተረጉም ይጸልይ።
14Nes jei meldžiuosi kalbomis, meldžiasi mano dvasia, bet protas lieka bevaisis.
14በልሳን ብጸልይ መንፈሴ ይጸልያል አእምሮዬ ግን ያለ ፍሬ ነው።
15Ką gi tada daryti? Melsiuosi dvasia ir melsiuosi protu; giedosiu dvasia ir giedosiu protu.
15እንግዲህ ምንድር ነው? በመንፈስ እጸልያለሁ በአእምሮም ደግሞ እጸልያለሁ፤ በመንፈስ እዘምራለሁ በአእምሮም ደግሞ እዘምራለሁ።
16Be to, jei tu laimini dvasia, kaip neišmanantis pasakys tavo padėkai “amen”, nesuprasdamas, ką tu kalbi?
16እንዲያማ ካልሆነ፥ አንተ በመንፈስ ብትባርክ ባልተማሩት ስፍራ የተቀመጠው የምትለውን ካላወቀ እንዴት አድርጎ ለምስጋናህ አሜን ይላል?
17Juk tu gražiai dėkoji, tačiau kitas nėra ugdomas.
17አንተማ መልካም ታመሰግናለህ፥ ሌላው ግን አይታነጽበትም።
18Dėkui mano Dievui, aš kalbu kalbomis daugiau už jus visus,
18ከሁላችሁ ይልቅ በልሳኖች እናገራለሁና እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤
19vis dėlto bažnyčioje geriau pasakysiu penkis žodžius savo protu, kad pamokyčiau ir kitus, negu tūkstančius žodžių kalbomis.
19ነገር ግን ሌሎችን ደግሞ አስተምር ዘንድ በማኅበር እልፍ ቃላት በልሳን ከመናገር ይልቅ አምስት ቃላት በአእምሮዬ ልናገር እወዳለሁ።
20Broliai! Nebūkite vaikai išmanymu. Verčiau blogybe būkite kūdikiai, bet išmanymu­subrendę.
20ወንድሞች ሆይ፥ በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ፤ ለክፋት ነገር ሕፃናት ሁኑ እንጂ በአእምሮ የበሰሉ ሁኑ።
21Įstatyme parašyta: “Svetimomis kalbomis ir svetimųjų lūpomis Aš kalbėsiu šiai tautai, bet ir tada jie nepaklausys manęs”,­sako Viešpats.
21ሌሎችን ልሳኖች በሚናገሩ ሰዎችና በሌላ አንደበት ለዚህ ሕዝብ እነግራቸዋለሁ፥ እንዲህም ቢሆን አይሰሙኝም ይላል ጌታ ተብሎ በሕግ ተጽፎአል።
22Todėl kalbos yra ženklas ne tikintiems, bet netikintiems. O pranašavimas­ne netikintiems, bet tikintiems.
22እንግዲያስ በልሳኖች መናገር ለማያምኑ ምልክት ነው እንጂ ለሚያምኑ አይደለም፥ ትንቢት ግን ለሚያምኑ እንጂ ለማያምኑ አይደለም።
23Juk jei susirinktų visa bažnyčia ir visi imtų kalbėti kalbomis, ir įeitų neišmanantys ar netikintys,­argi jie nesakytų, kad jūs išėję iš proto?
23እንግዲህ ማኅበር ሁሉ አብረው ቢሰበሰቡ ሁሉም በልሳኖች ቢናገሩና ያልተማሩ ወይም የማያምኑ ሰዎች ቢገቡ። አብደዋል አይሉምን?
24Bet jeigu visi pranašautų ir įeitų netikintis ar neišmanantis, jis būtų visų apkaltintas ir visų atpažintas.
24ሁሉ ትንቢት ቢናገሩ ግን የማያምን ወይም ያልተማረ ሰው ቢገባ በሁሉ ይወቀሳል፥ በሁሉም ይመረመራል፤
25Jo širdies paslaptys būtų atskleistos, ir jis, puolęs veidu žemėn, pagarbintų Dievą ir išpažintų: “Dievas iš tiesų yra tarp jūsų!”
25በልቡም የተሰወረ ይገለጣል እንዲሁም። እግዚአብሔር በእውነት በመካከላቸው ነው ብሎ እየተናገረ በፊቱ ወድቆ ለእግዚአብሔር ይሰግዳል።
26Tad kaip bus, broliai? Kai susirenkate, kiekvienas turi giesmę ar pamokymą, ar kalbą, ar apreiškimą, ar aiškinimą. Tegul viskas tarnauja ugdymui.
26እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ምንድር ነው? በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለእያንዳንዱ መዝሙር አለው፥ ትምህርት አለው፥ መግለጥ አለው፥ በልሳን መናገር አለው፥ መተርጐም አለው፤ ሁሉ ለማነጽ ይሁን።
27Jei kalba kas kalbomis, tekalba du, daugiausia trys, paeiliui, o vienas tegul aiškina.
27በልሳን የሚናገር ቢኖር ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው በተራቸው ይናገሩ አንዱም ይተርጉም፤
28Bet jeigu nėra aiškintojo, tegul tas bažnyčioje tyli ir tekalba tik sau ir Dievui.
28የሚተረጉም ባይኖር ግን በማኅበር መካከል ዝም ይበልና ለራሱና ለእግዚአብሔር ይናገር።
29Ir pranašai tekalba du ar trys, o kiti teapsvarsto.
29ነቢያትም ሁለት ወይም ሦስት ሆነው ይናገሩ ሌሎችም ይለዩአቸው፤
30Bet jei kitam šalia sėdinčiam kas nors apreiškiama, pirmasis tenutyla.
30በዚያ ለሚቀመጥ ለሌላ ግን አንድ ነገር ቢገለጥለት ፊተኛው ዝም ይበል።
31Nes jūs visi galite vienas po kito pranašauti, kad visi pasimokytų ir visi būtų paguosti.
31ሁሉም እንዲማሩ ሁሉም እንዲመከሩ ሁላችሁ በእያንዳንዳችሁ ትንቢት ልትናገሩ ትችላላችሁ።
32Pranašų dvasios yra paklusnios pranašams,
32የነቢያትም መናፍስት ለነቢያት ይገዛሉ፤
33nes Dievas nėra sumaišties, bet ramybės Dievas,­kaip ir visose šventųjų bažnyčiose.
33እግዚአብሔርስ የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለምና፤ በቅዱሳንም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንዲህ ነው።
34Jūsų moterys bažnyčiose tetyli, nes joms neleidžiama kalbėti, jos turi būti klusnios, kaip sako ir įstatymas.
34ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፤ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።
35Ir jeigu jos nori ko nors išmokti, tepasiklausia namie savo vyro, nes moterims gėdinga bažnyčioje kalbėti.
35ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር ነውና፥ ምንም ሊማሩ ቢወዱ በቤታቸው ባሎቻቸውን ይጠይቁ።
36Argi iš jūsų išėjo Dievo žodis? Ar tik jus vienus pasiekė?
36ምን ነው? የእግዚአብሔር ቃል የወጣ ከእናንተ ነውን? ወይስ ወደ እናንተ ብቻ ደርሶአልን?
37Jei kas mano esąs pranašas ar dvasinis žmogus, tegu pripažįsta, kad tai, ką jums rašau, yra Viešpaties įsakymai.
37ማንም ነቢይ ወይም መንፈሳዊ የሆነ ቢመስለው ይህች የጻፍሁላችሁ የጌታ ትእዛዝ እንደ ሆነች ይወቅ፤
38Bet jei kas neišmano, tegul neišmano.
38ማንም የማያውቅ ቢኖር ግን አይወቅ።
39Todėl, broliai, karštai trokškite pranašauti ir nedrauskite kalbėti kalbomis.
39ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ትንቢት ለመናገር በብርቱ ፈልጉ፥ በልሳኖች ከመናገርም አትከልክሉ፤
40Tebūnie viskas daroma padoriai ir tvarkingai.
40ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።