1Jeigu aš kalbu žmonių ir angelų kalbomis, bet neturiu meilės, esu kaip skambantis varis ar žvangantys cimbolai.
1በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ።
2Ir jei turiu pranašavimo dovaną ir suprantu visas paslaptis, ir turiu visą pažinimą; jei turiu visą tikėjimą, kad galiu kalnus perkelti, tačiau neturiu meilės, esu niekas.
2ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።
3Ir jei išdalinu vargšams pamaitinti visa, ką turiu, ir jeigu atiduodu savo kūną sudeginti, bet neturiu meilės,man nėra iš to jokios naudos.
3ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል፥ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም።
4Meilė kantri ir maloni, meilė nepavydi; meilė nesigiria ir neišpuiksta.
4ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤
5Ji nesielgia nepadoriai, neieško savo naudos, nepasiduoda piktumui, nemąsto piktai,
5የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም፤
6nesidžiaugia neteisybe, džiaugiasi tiesa;
6ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፤
7visa pakenčia, visa tiki, viskuo viliasi ir visa ištveria.
7ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል።
8Meilė niekada nesibaigia. Baigsis pranašystės, paliaus kalbos, išnyks pažinimas,
8ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል።
9nes mes žinome iš dalies ir mes pranašaujame iš dalies.
9ከእውቀት ከፍለን እናውቃለንና፥ ከትንቢትም ከፍለን እንናገራለንና፤
10Bet kai ateis tobulumas, tai, kas iš dalies, pasibaigs.
10ፍጹም የሆነ ሲመጣ ግን ተከፍሎ የነበረው ይሻራል።
11Kai buvau vaikas, kalbėjau kaip vaikas, supratau kaip vaikas, mąsčiau kaip vaikas, bet tapęs vyru, palikau tai, kas vaikiška.
11ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እናገር ነበር፥ እንደ ልጅም አስብ ነበር፥ እንደ ልጅም እቈጥር ነበር፤ ጎልማሳ ሆኜ ግን የልጅነትን ጠባይ ሽሬአለሁ።
12Dabar mes matome kaip per stiklą, miglotai, bet tadaveidas į veidą. Dabar žinau iš dalies, bet tada pažinsiu, kaip ir pats esu pažintas.
12ዛሬስ በመስተዋት በድንግዝግዝ እንደምናይ ነን በዚያን ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን፤ ዛሬስ ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ በዚያን ጊዜ ግን እኔ ደግሞ እንደ ታወቅሁ አውቃለሁ።
13Taigi dabar pasilieka tikėjimas, viltis ir meilėšis trejetas, bet didžiausia iš jų yra meilė.
13እንዲህም ከሆነ፥ እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ከእነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው።