Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Corinthians

12

1Aš nenoriu, broliai, kad jūs neišmanytumėte apie dvasines dovanas.
1ስለ መንፈሳዊ ነገርም፥ ወንድሞች ሆይ፥ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ።
2Jūs žinote, kad, kai buvote pagonys, ėjote prie nebylių stabų kaip vedami.
2አሕዛብ ሳላችሁ በማናቸውም ጊዜ እንደምትመሩ ድምፅ ወደሌላቸው ወደ ጣዖታት እንደ ተወሰዳችሁ ታውቃላችሁ።
3Todėl aš jums aiškinu, kad nė vienas, kuris kalba Dievo Dvasia, neprakeikia Jėzaus. Ir nė vienas negali sakyti, kad Jėzus yra Viešpats, kaip tik Šventąja Dvasia.
3ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ ሲናገር። ኢየሱስ የተረገመ ነው የሚል እንደሌለ፥ በመንፈስ ቅዱስም ካልሆነ በቀር። ኢየሱስ ጌታ ነው ሊል አንድ እንኳ እንዳይችል አስታውቃችኋለሁ።
4Yra skirtingų dovanų, tačiau ta pati Dvasia.
4የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤
5Yra skirtingų tarnavimų, tačiau tas pats Viešpats.
5አገልግሎትም ልዩ ልዩ ነው ጌታም አንድ ነው፤
6Ir yra skirtingi veiksmai, tačiau tas pats Dievas, kuris visa veikia visame kame.
6አሠራርም ልዩ ልዩ ነው፥ ሁሉን በሁሉ የሚያደርግ እግዚአብሔር ግን አንድ ነው።
7Bet kiekvienam suteikiamas Dvasios pasireiškimas bendram labui.
7ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን መግለጥ ለእያንዳንዱ ለጥቅም ይሰጠዋል።
8Vienam Dvasia suteikiamas išminties žodis, kitam ta pačia Dvasia­pažinimo žodis,
8ለአንዱ ጥበብን መናገር በመንፈስ ይሰጠዋልና፥ ለአንዱም በዚያው መንፈስ እውቀትን መናገር ይሰጠዋል፥
9kitam­tikėjimas ta pačia Dvasia, kitam­išgydymų dovanos ta pačia Dvasia,
9ለአንዱም በዚያው መንፈስ እምነት፥ ለአንዱም በአንዱ መንፈስ የመፈወስ ስጦታ፥ ለአንዱም ተአምራትን ማድረግ፥
10kitam­stebuklų darymas, kitam­pranašavimas, kitam­dvasių atpažinimas, kitam­skirtingos kalbos, kitam­kalbų aiškinimas.
10ለአንዱም ትንቢትን መናገር፥ ለአንዱም መናፍስትን መለየት፥ ለአንዱም በልዩ ዓይነት ልሳን መናገር፥ ለአንዱም በልሳኖች የተነገረውን መተርጎም ይሰጠዋል፤
11Bet visa tai daro viena ir ta pati Dvasia, kuri dalija kiekvienam atskirai, kaip Jai patinka.
11ይህን ሁሉ ግን ያ አንዱ መንፈስ እንደሚፈቅድ ለእያንዳንዱ ለብቻው እያካፈለ ያደርጋል።
12Nes kaip kūnas yra vienas ir turi daug narių, o visi to vieno kūno nariai, nepaisant daugumo, sudaro vieną kūną, taip ir Kristus.
12አካልም አንድ እንደ ሆነ ብዙም ብልቶች እንዳሉበት ነገር ግን የአካል ብልቶች ሁሉ ብዙዎች ሳሉ አንድ አካል እንደ ሆኑ፥ ክርስቶስ ደግሞ እንዲሁ ነው፤
13Nes viena Dvasia mes visi esame pakrikštyti į vieną kūną,­žydai ar graikai, vergai ar laisvieji; ir visi buvome pagirdyti viena Dvasia.
13አይሁድ ብንሆን የግሪክ ሰዎችም ብንሆን ባሪያዎችም ብንሆን ጨዋዎችም ብንሆን እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናልና። ሁላችንም አንዱን መንፈስ ጠጥተናል።
14Juk kūnas nėra sudėtas iš vieno nario, bet iš daugelio.
14አካል ብዙ ብልቶች እንጂ አንድ ብልት አይደለምና።
15Jei koja sakytų: “Kadangi nesu ranka, todėl nepriklausau kūnui”, argi dėl to ji nepriklausytų kūnui?
15እግር። እኔ እጅ አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ብትል፥ ይህን በማለትዋ የአካል ክፍል መሆንዋ ይቀራልን?
16O jeigu ausis sakytų: “Kadangi nesu akis, todėl nepriklausau kūnui”, argi dėl to ji nepriklausytų kūnui?
16ጆሮም። እኔ ዓይን አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ቢል፥ ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን?
17Jeigu visas kūnas būtų akis, tai kur būtų klausa? Jeigu visas kūnas būtų klausa, tai kur būtų uoslė?
17አካል ሁሉ ዓይን ቢሆን መስማት ወዴት በተገኘ? ሁሉም መስማት ቢሆን ማሽተት ወዴት በተገኘ?
18Bet dabar Dievas sudėliojo kūne narius ir kiekvieną iš jų, kaip panorėjo.
18አሁን ግን እግዚአብሔር እንደ ወደደ ብልቶችን እያንዳንዳቸው በአካል አድርጎአል።
19Ir jei visi būtų vienas narys, kur beliktų kūnas?
19ሁሉም አንድ ብልት ቢሆንስ አካል ወዴት በሆነ?
20Bet dabar narių daug, o kūnas vienas.
20ዳሩ ግን አሁን ብልቶች ብዙዎች ናቸው አካል ግን አንድ ነው።
21Akis negali pasakyti rankai: “Man tavęs nereikia”, ar galva kojoms: “Man jūsų nereikia”.
21ዓይን እጅን። አታስፈልገኝም ልትለው አትችልም፥ ወይም ራስ ደግሞ እግሮችን። አታስፈልጉኝም ሊላቸው አይችልም።
22Priešingai, tie kūno nariai, kurie atrodo silpnesni, yra būtini.
22ነገር ግን ደካሞች የሚመስሉ የአካል ብልቶች ይልቁን የሚያስፈልጉ ናቸው፤
23Tuos kūno narius, kuriuos laikome mažiau garbingais, mes apsupame didesne pagarba, ir mūsų gėdingi nariai gaubiami didesnio padorumo,
23ከአካልም ብልቶች ያልከበሩ ሆነው የሚመስሉን በሚበዛ ክብር እናለብሳቸዋለን፥ በምናፍርባቸውም ብልቶቻችን ክብር ይጨመርላቸዋል፤
24kurio nereikia mūsų padoriesiems nariams. Taigi, tvarkydamas kūną, Dievas skyrė daugiau pagarbos tiems kūno nariams, kurie jos stokojo,
24ክብር ያላቸው ብልቶቻችን ግን ይህ አያስፈልጋቸውም። ነገር ግን ብልቶች እርስ በርሳቸው በትክክል ይተሳሰቡ ዘንድ እንጂ በአካል መለያየት እንዳይሆን፥ ለጎደለው ብልት የሚበልጥ ክብር እየሰጠ እግዚአብሔር አካልን አገጣጠመው።
25kad kūne nebūtų susiskaldymų, bet patys nariai rūpintųsi vieni kitais.
26አንድም ብልት ቢሣቀይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሣቀያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል።
26Todėl, jei kenčia vienas narys, su juo kenčia ir visi nariai. Ir jei kuris narys pagerbiamas, su juo džiaugiasi visi nariai.
27እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ እያንዳንዳችሁም ብልቶች ናችሁ።
27Jūs esate Kristaus kūnas, o pavieniui­nariai.
28እግዚአብሔርም በቤተ ክርስቲያን አንዳንዶቹን አስቀድሞ ሐዋርያትን፥ ሁለተኛም ነቢያትን፥ ሦስተኛም አስተማሪዎችን፥ ቀጥሎም ተአምራት ማድረግን፥ ቀጥሎም የመፈወስን ስጦታ፥ እርዳታንም፥ አገዛዝንም፥ የልዩ ልዩ ዓይነት ልሳኖችንም አድርጎአል።
28Ir šiuos Dievas paskyrė bažnyčioje: pirma­apaštalais, antra­pranašais, trečia­mokytojais; po to­ stebuklai, paskui­išgydymų dovanos, visokia pagalba, vadovavimai, įvairios kalbos.
29ሁሉ ሐዋርያት ናቸውን? ሁሉስ ነቢያት ናቸውን? ሁሉስ አስተማሪዎች ናቸውን? ሁሉስ ተአምራትን ይሠራሉን?
29Ar visi apaštalai? Ar visi pranašai? Ar visi mokytojai? Ar visi stebukladariai?
30ሁሉስ የመፈወስ ስጦታ አላቸውን? ሁሉስ በልሳኖች ይናገራሉን? ሁሉስ ይተረጉማሉን?
30Ar visi turi išgydymų dovanas? Ar visi kalba kalbomis? Ar visi aiškina?
31ነገር ግን የሚበልጠውን የጸጋ ስጦታ በብርቱ ፈልጉ። ደግሞም ከሁሉ የሚበልጥ መንገድ አሳያችኋለሁ።
31Taigi karštai trokškite aukštesniųjų dovanų! Ir visgi rodau jums dar pranašesnį kelią.