Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Corinthians

11

1Sekite manimi, kaip ir aš seku Kristumi.
1እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።
2Aš jus giriu, kad visame kame prisimenate mane ir laikotės nurodymų, kuriuos jums daviau.
2ወንድሞች ሆይ፥ በሁሉ ስለምታስቡኝና አሳልፌ እንደ ሰጠኋችሁ ወግን ፈጽማችሁ ስለ ያዛችሁ አመሰግናችኋለሁ።
3Noriu, kad žinotumėte, jog kiekvieno vyro galva yra Kristus, moters galva­vyras, o Kristaus galva­Dievas.
3ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ።
4Kiekvienas vyras, kuris meldžiasi ar pranašauja apdengta galva, paniekina savo galvą.
4ራሱን ተከናንቦ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ወንድ ሁሉ ራሱን ያዋርዳል።
5Ir kiekviena moteris, kuri meldžiasi ar pranašauja neapdengta galva, paniekina savo galvą: tai tas pats, kaip būti nuskustai.
5ራስዋን ሳትሸፍን ግን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ሁሉ ራስዋን ታዋርዳለች፤ እንደ ተላጨች ያህል አንድ ነውና።
6Jei moteris neapsigaubia, tai tegul ir nusikerpa! O jei moteriai gėda nusikirpti ar nusiskusti plaukus, teapsigaubia.
6ሴትም ራስዋን ባትሸፍን ጠጉርዋን ደግሞ ትቆረጥ፤ ለሴት ግን ጠጉርዋን መቆረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ከሆነ ራስዋን ትሸፍን።
7Vyrui nereikia gaubti galvos, nes jis yra Dievo atvaizdas ir šlovė. O moteris yra vyro šlovė.
7ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ስለ ሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም፤ ሴት ግን የወንድ ክብር ናት።
8Juk ne vyras iš moters, bet moteris iš vyro,
8ሴት ከወንድ ናት እንጂ ወንድ ከሴት አይደለምና።
9taip pat ne vyras buvo sukurtas moteriai, o moteris vyrui.
9ሴት ስለ ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ ስለ ሴት አልተፈጠረምና።
10Todėl moteris privalo turėti ant galvos pavaldumo ženklą dėl angelų.
10ስለዚህ ሴት ከመላእክት የተነሣ በራስዋ ሥልጣን ሊኖራት ይገባል።
11Bet Viešpatyje nei vyras be moters, nei moteris be vyro.
11ነገር ግን በጌታ ዘንድ ሴት ያለ ወንድ ወንድም ያለ ሴት አይሆንም።
12Kaip moteris iš vyro, taip vyras per moterį, bet visa­iš Dievo.
12ሴት ከወንድ እንደ ሆነች እንዲሁ ወንድ ደግሞ በሴት ነውና፤ ሁሉም ከእግዚአብሔር ነው።
13Spręskite patys: argi tinka moteriai melstis Dievui neapsigaubusiai?
13በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት ራስዋን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን?
14Argi pati prigimtis jūsų nemoko, jog vyrui gėda nešioti ilgus plaukus?
14ወንድ ጠጉሩን ቢያስረዝም ነውር እንዲሆንበት፥ ሴት ግን ጠጉርዋን ብታስረዝም ክብር እንዲሆንላት ተፈጥሮ እንኳ አያስተምራችሁምን? ጠጉርዋ መጎናጸፊያ ሊሆን ተሰጥቶአታልና።
15Tuo tarpu moteriai garbė turėti ilgus plaukus. Nes plaukai jai duoti kaip dangalas.
16ዳሩ ግን ማንም ሊከራከር ቢፈቅድ፥ እኛ ወይም የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ያለ ልማድ የለንም።
16Bet jei kas norėtų ginčytis,­težino, jog nei mes, nei Dievo bažnyčios neturime tokio papročio.
17ነገር ግን በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለሚከፋ እንጂ ለሚሻል ስላልሆነ ይህን ትእዛዝ ስሰጥ የማመሰግናችሁ አይደለም።
17Duodamas šiuos nurodymus, aš jūsų negiriu, nes jūsų susirinkimai išeina ne į gera, bet į bloga.
18በመጀመሪያ ወደ ማኅበር ስትሰበሰቡ በመካከላችሁ መለያየት እንዳለ እሰማለሁና፥ በአንድ በኩልም አምናለሁ።
18Pirmiausia man teko girdėti, kad, kai jūs susirenkate bažnyčioje, tarp jūsų būna susiskaldymų, ir iš dalies aš tuo tikiu.
19በእናንተ ዘንድ የተፈተኑት እንዲገለጡ በመካከላችሁ ወገኖች ደግሞ ሊሆኑ ግድ ነውና።
19Juk pas jus turi būti atskalų, kad išaiškėtų tie, kurie yra patikimi.
20እንግዲህ አብራችሁ ስትሰበሰቡ የምትበሉት የጌታ እራት አይደለም፤
20Jūs susirenkate kartu, bet ne Viešpaties vakarienės valgyti,
21በመብላት ጊዜ እያንዳንዱ የራሱን እራት ይበላልና፥ አንዱም ይራባል አንዱ ግን ይሰክራል።
21nes kiekvienas paskuba suvalgyti savo maistą, ir vienas lieka alkanas, o kitas nusigeria.
22የምትበሉባቸውና የምትጠጡባቸው ቤቶች የላችሁምን? ወይስ የእግዚአብሔርን ማኅበር ትንቃላችሁን አንዳችም የሌላቸውን ታሳፍራላችሁን? ምን ልበላችሁ? በዚህ ነገር ላመስግናችሁን? አላመሰግናችሁም።
22Argi neturite savo namų valgyti ir gerti? O gal norite paniekinti Dievo bažnyčią ir sugėdinti stokojančius? Kas man belieka sakyti? Pagirti? Ne! Už tai nepagirsiu.
23ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠሁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለሁና፤
23Aš tai gavau iš Viešpaties ir perdaviau jums, kad Viešpats Jėzus tą naktį, kurią buvo išduotas, paėmė duoną
24ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም። እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
24ir padėkojęs sulaužė ir tarė: “Imkite ir valgykite; tai yra mano kūnas, kuris už jus sulaužomas. Tai darykite mano atminimui”.
25እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ። ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
25Taip pat po vakarienės jis paėmė taurę ir tarė: “Ši taurė yra Naujoji Sandora mano kraujyje. Kiek kartų gersite, darykite tai mano atminimui”.
26ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና።
26Taigi, kada tik valgote šitą duoną ir geriate šitą taurę, jūs skelbiate Viešpaties mirtį, kol Jis ateis.
27ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት።
27Todėl kas nevertai valgo tos duonos ir geria iš Viešpaties taurės, tas bus kaltas prieš Viešpaties kūną ir kraują.
28ሰው ግን ራሱን ይፈትን፥ እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤
28Teištiria žmogus pats save ir tada tevalgo tos duonos ir tegeria iš tos taurės.
29ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና።
29Nes kas valgo ir geria nevertai, Viešpaties kūno neišskirdamas, tas valgo ir geria sau pasmerkimą.
30ስለዚህ በእናንተ ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ አያሌዎችም አንቀላፍተዋል።
30Todėl tarp jūsų daug silpnų bei ligotų ir daug užmigusių.
31ራሳችንን ብንመረምር ግን ባልተፈረደብንም ነበር፤
31Jei mes patys save teistume, nebūtume teisiami.
32ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን።
32Bet kai Viešpats mus teisia, tai ir sudraudžia, kad nebūtume pasmerkti kartu su pasauliu.
33ስለዚህ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ ለመብላት በተሰበሰባችሁ ጊዜ እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ።
33Todėl, mano broliai, kai susirenkate valgyti, palaukite vieni kitų.
34ማንም የራበው ቢኖር ለፍርድ እንዳትሰበሰቡ በቤቱ ይብላ። የቀረውንም ነገር በመጣሁ ጊዜ እደነግጋለሁ።
34O jeigu kas išalkęs, tepavalgo namie, kad nesirinktumėte pasmerkimui. Kitus reikalus sutvarkysiu atvykęs.