1Aš nenoriu, kad liktumėte nežinioje, broliai,visi mūsų tėvai buvo po debesim ir visi perėjo jūrą.
1ወንድሞች ሆይ፥ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ። አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ ሁሉም በባሕር መካከል ተሻገሩ፤
2Ir visi buvo pakrikštyti į Mozę, debesyje ir jūroje;
2ሁሉም ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ በደመናና በባሕር ተጠመቁ፤
3visi valgė tą patį dvasinį maistą
3ሁሉም ያን መንፈሳዊ መብል በሉ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ፤
4ir visi gėrė tą patį dvasinį gėrimą. Jie gėrė iš dvasinės juos lydinčios uolos, o ta uola buvo Kristus.
4ይከተላቸው ከነበረው ከመንፈሳዊ ዓለት ጠጥተዋልና፥ ያም ዓለት ክርስቶስ ነበረ።
5Vis dėlto daugumas iš jų nepatiko Dievui, ir “jų kūnai liko gulėti dykumoje”.
5እግዚአብሔር ግን ከእነርሱ በሚበዙት ደስ አላለውም፥ በምድረ በዳ ወድቀዋልና።
6Tie įvykiai yra mums pavyzdžiai, kad negeistume blogio, kaip anie geidė.
6እነዚህም ክፉ ነገር እንደ ተመኙ እኛ ደግሞ እንዳንመኝ ይህ ምሳሌ ሆነልን።
7Nebūkite stabmeldžiai, kaip kai kurie iš jų,kaip parašyta: “Tauta sėdosi valgyti ir gerti ir kėlėsi žaisti”.
7ሕዝብም ሊበሉ ሊጠጡም ተቀመጡ ሊዘፍኑም ተነሡ ተብሎ እንደ ተጻፈ ከእነርሱ አንዳንዶቹ እንዳደረጉት ጣዖትን የምታመልኩ አትሁኑ።
8Neištvirkaukime, kaip kai kurie iš jų ištvirkavo ir žuvo vieną dieną dvidešimt trys tūkstančiai.
8ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንደ ሴሰኑ በአንድ ቀንም ሁለት እልፍ ከሦስት ሺህ እንደ ወደቁ አንሴስን።
9Negundykime Kristaus, kaip kai kurie iš jų gundė ir mirė nuo gyvačių.
9ከእነርሱም አንዳንዶቹ ጌታን እንደ ተፈታተኑት በእባቦቹም እንደ ጠፉ ጌታን አንፈታተን።
10Nemurmėkite, kaip kai kurie iš jų murmėjo ir žuvo nuo naikintojo.
10ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንዳንጎራጎሩ በሚያጠፋውም እንደ ጠፉ አታንጐርጕሩ።
11Visa tai jiems atsitiko kaip pavyzdžiai, ir užrašyti pamokyti mums, gyvenantiems amžių pabaigoje.
11ይህም ሁሉ እንደ ምሳሌ ሆነባቸው፥ እኛንም የዘመናት መጨረሻ የደረሰብንን ሊገሥጸን ተጻፈ።
12Todėl, kas tariasi stovįs, težiūri, kad nekristų.
12ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።
13Jums tekęs pagundymas tėra tik žmogiškas. Bet Dievas ištikimas. Jis neleis jūsų gundyti daugiau nei jūsų jėgos leidžia, bet kartu su pagundymu duos ir išeitį, kad sugebėtumėte jį atlaikyti.
13ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።
14Todėl, mano mylimieji, bėkite nuo stabmeldystės!
14ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ።
15Kalbu kaip išmintingiems; apsvarstykite patys, ką sakau.
15ልባሞች እንደ መሆናችሁ እላለሁ፤ በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ።
16Argi laiminimo taurė, kurią laiminame, nėra bendravimas Kristaus kraujyje? Argi duona, kurią laužome, nėra bendravimas Kristaus kūne?
16የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን?
17Nors mūsų daug, mes visi esame viena duona ir vienas kūnas: juk mes visi dalijamės viena duona.
17አንድ እንጀራ ስለ ሆነ፥ እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን፤ ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና።
18Pažiūrėkite į Izraelį pagal kūną: argi tie, kurie valgo aukas, nėra aukuro bendrininkai?
18በሥጋ የሆነውን እስራኤል ተመልከቱ፤ መሥዋዕቱን የሚበሉ የመሠዊያው ማኅበረተኞች አይደሉምን?
19Ką gi sakau? Ar stabas ką nors reiškia? Ar ką nors reiškia auka stabams?
19እንግዲህ ምን እላለሁ? ለጣዖት የተሠዋ ምናምን ነው እላለሁን? ወይስ ጣዖት ምናምን እንዲሆን እላለሁን?
20Ne, bet pagonys, aukodami aukas, aukoja demonams, o ne Dievui. Ir aš nenoriu, kad jūs būtumėte demonų bendrininkai.
20አይደለም፤ ነገር ግን አሕዛብ የሚሠዉት ለአጋንንት እንዲሆን እንጂ ለእግዚአብሔር እንዳይሠዉ እላለሁ፤ ከአጋንንትም ጋር ማኅበረተኞች እንድትሆኑ አልወድም።
21Jūs negalite gerti Viešpaties taurės ir demonų taurės. Negalite sėdėti prie Viešpaties stalo ir prie demonų stalo.
21የጌታን ጽዋና የአጋንንትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፤ ከጌታ ማዕድና ከአጋንንት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም።
22Nejaugi kurstysime Viešpaties pavydą? Ar mes už Jį stipresni?
22ወይስ ጌታን እናስቀናውን? እኛስ ከእርሱ ይልቅ እንበረታለንን?
23Viskas man leistina, bet ne viskas naudinga. Viskas man leistina, bet ne viskas ugdo!
23ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።
24Niekas teneieško, kaip jam geriau, bet kaip kitam.
24እያንዳንዱ የባልንጀራውን ጥቅም እንጂ አንድ ስንኳ የራሱን ጥቅም አይፈልግ።
25Valgykite visa, kas parduodama mėsos prekyvietėje, sąžinės labui nieko neklausinėdami.
25በሥጋ ገበያ የሚሸጠውን ሁሉ ከሕሊና የተነሣ ሳትመራመሩ ብሉ፤
26Juk “Viešpaties yra žemė ir visa, ko ji pilna”.
26ምድርና በእርስዋ የሞላባት ሁሉ የጌታ ነውና።
27Jeigu jus pasikviečia netikintis žmogus ir jūs norite jį aplankyti, valgykite visa, kas jums padedama, sąžinės labui nieko neklausinėdami.
27ከማያምኑ ሰዎች አንዱም ቢጠራችሁ ልትሄዱም ብትወዱ ከሕሊና የተነሣ ሳትመራመሩ የሚያቀርቡላችሁን ሁሉ ብሉ።
28Bet jei kas jums pasakytų: “Tai auka stabams”, tada nevalgykite dėl žmogaus, kuris tai pasakė, ir dėl sąžinės,juk “Viešpaties yra žemė ir visa, ko ji pilna”.
28ማንም ግን። ይህ ለጣዖት የተሠዋ ነው ቢላችሁ ከዚያ ካስታወቃችሁና ከሕሊና የተነሣ አትብሉ፤
29Čia aš kalbu ne apie tavo paties sąžinę, bet apie kito sąžinę. Kodėl gi mano laisvė turėtų būti teisiama kitos sąžinės?
29ስለ ባልንጀራህ ሕሊና እንጂ ስለ ገዛ ሕሊናህ አልናገርም። አርነቴ በሌላ ሰው ሕሊና የሚፈርድ Avረ ስለ ምንድር ነው?
30Jeigu aš dėkodamas valgau, kodėl man priekaištaujama dėl maisto, už kurį dėkoju?
30እኔም በጸጋ ብበላ፥ በነገሩ ስለማመሰግንበት ስለ ምን እሰደባለሁ?
31Todėl ar valgote, ar geriate, ar šiaip ką darote, visa darykite Dievo šlovei.
31እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።
32Nepiktinkite nei žydų, nei graikų, nei Dievo bažnyčios,
32እኔ ደግሞ ብዙዎቹ ይድኑ ዘንድ ለጥቅማቸው እንጂ የራሴን ጥቅም ሳልፈልግ በሁሉ ነገር ሰውን ሁሉ ደስ እንደማሰኝ፥ ለአይሁድም ለግሪክም ሰዎች ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንም ማሰናከያ አትሁኑ።
33kaip ir aš stengiuosi visiems viskuo patikti, neieškodamas sau naudos, bet to, kas naudinga daugeliui, kad jie būtų išgelbėti.