Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Corinthians

9

1Ar aš ne apaštalas? Ar aš ne laisvas? Ar nesu regėjęs Jėzaus Kristaus, mūsų Viešpaties? Ar jūs ne mano darbo vaisius Viešpatyje?
1እኔ ነጻ አይደለሁምን? ሐዋርያስ አይደለሁምን? ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንስ አላየሁትምን? እናንተስ በጌታ ሥራዬ አይደላችሁምን?
2Jei kitiems ir nesu apaštalas, tai jums, be abejo, esu, nes mano apaštalystės antspaudas esate jūs Viešpatyje.
2የሐዋርያነቴ ማኅተም በጌታ እናንተ ናችሁና ለሌሎች ሐዋርያ ባልሆን ለእናንተስ ምንም ቢሆን ሐዋርያ ነኝ።
3Štai mano pasiteisinimas prieš tuos, kurie mane kaltina.
3ለሚመረምሩኝ መልሴ ይህ ነው። ልንበላና ልንጠጣ መብት የለንምን?
4Argi mes neturime teisės valgyti ir gerti?
5እንደ ሌሎቹ ሐዋርያትና እንደ ጌታ ወንድሞች እንደ ኬፋም፥ እኅት ሚስታችንን ይዘን ልንዞር መብት የለንምን?
5Ar neturime teisės vaikščioti kartu su seserimi, žmona, kaip kiti apaštalai ir Viešpaties broliai bei Kefas?
6ወይስ ሥራን ለመተው መብት የሌለን እኔና በርናባስ ብቻ ነን?
6O gal tik aš ir Barnabas neturime teisės nedirbti?
7ከቶ በገዛ ገንዘቡ በወታደርነት የሚያገለግል ማን ነው? ወይስ ወይን ተክሎ ፍሬውን የማይበላ ማን ነው? ወይስ መንጋ እየጠበቀ ከመንጋው ወተት የማይጠጣ ማን ነው?
7Kas gi tarnauja kariuomenėje už savo paties pinigus? Kas sodina vynuogyną ir nevalgo jo vaisių? Arba kas gano bandą ir negeria bandos pieno?
8ይህን በሰው ሥልጣን ብቻ እላለሁን?
8Ar aš tai sakau vien kaip žmogus? Argi to paties nesako ir Įstatymas?
9ሕግስ ደግሞ ያን አይልምን? የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር ተብሎ በሙሴ ሕግ ተጽፎአልና። እግዚአብሔርስ ስለ በሬዎች ይገደዋልን?
9Mozės Įstatyme parašyta: “Neužrišk nasrų kuliančiam jaučiui!” Bet ar Dievui terūpi jaučiai?
10ይህን የሚለው ፈጽሞ ስለ እኛ አይደለምን? የሚያርስ በተስፋ ሊያርስ የሚያበራይም እንዲካፈል በተስፋ ሊያበራይ ስለሚገባው በእውነት ስለ እኛ ተጽፎአል።
10O gal Jis iš tiesų taiko tai mums? Juk dėl mūsų parašyta, kad artojas artų su viltimi ir kūlėjas kultų su viltimi, jog gaus savo dalį.
11እኛ መንፈሳዊን ነገር የዘራንላችሁ ከሆንን የእናንተን የሥጋዊን ነገር እኛ ብናጭድ ትልቅ ነገር ነውን?
11Jei mes jums pasėjome dvasinių gėrybių, tai ar didelis dalykas, kad pjausime pas jus medžiaginių?
12ሌሎች በእናንተ ላይ ይህን መብት የሚካፈሉ ከሆኑ እኛማ ይልቁን እንዴታ? ነገር ግን የክርስቶስን ወንጌል እንዳንከለክል በሁሉ እንታገሣለን እንጂ በዚህ መብት አልተጠቀምንም።
12Jei kiti turi teisių į jus, tai ar ne juo labiau mes? Vis dėlto mes nesinaudojome savo teise, bet viską pakeliame, kad tik Kristaus Evangelijai nedarytume kliūčių.
13በመቅደስ ነገር የሚያገለግሉ ከመቅደስ የሆነውን ነገርን እንዲመገቡ፥ በመሠዊያውም የሚጸኑ ከመሠዊያው እንዲካፈሉ አታውቁምን?
13Ar nežinote, kad tie, kurie tarnauja šventykloje, valgo iš šventyklos pajamų ir kad aukuro tarnai gauna dalį aukų?
14እንዲሁ ደግሞ ወንጌልን የሚሰብኩ ከወንጌል ቀለብ እንዲቀበሉ ጌታ ደንግጎአል።
14Taip ir Viešpats patvarkė, kad Evangelijos skelbėjai gyventų iš Evangelijos.
15እኔ ግን ከእነዚህ ሁሉ ምንም አልተጠቀምሁም። እንዲህ እንዲሆንልኝ ይህን አልጽፍም፤ ማንም ትምክህቴን ከንቱ ከሚያደርግብኝ ሞት ይሻለኛልና።
15Bet aš nesinaudojau šiomis teisėmis. Ir tai rašau ne tam, kad sau pritaikyčiau. Man geriau mirti, negu leisti, kad kas atimtų iš manęs šį pasigyrimą.
16ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።
16Jeigu skelbiu Evangeliją, neturiu pagrindo girtis, nes tai mano būtina pareiga, ir vargas man, jei Evangelijos neskelbčiau!
17ይህን በፈቃዴ ባደርገው ደመወዝ አለኝና፤ ያለ ፈቃዴ ግን ባደርገው መጋቢነት በአደራ ተሰጥቶኛል።
17Jeigu tai darau savo valia, turiu atlygį; bet jei darau ne savo valia, tai atlieku man patikėtą tarnavimą.
18እንግዲህ ደመወዜ ምንድር ነው? ወንጌልን እየሰበክሁ በወንጌል ካለኝ መብት በሙሉ እንዳልጠቀም ወንጌልን ያለ ዋጋ ብናገር ነው።
18Koks tada mano atlygis? Ogi kad, skelbdamas Kristaus Evangeliją, pateikiu ją veltui ir nesinaudoju savo teise, kurią man duoda Evangelijos skelbimas.
19ከሰው ሁሉ አርነት የወጣሁ ስሆን የሚበልጡትን እንድጠቅም እንደ ባሪያ ራሴን ለሁሉ አስገዛለሁ።
19Būdamas nuo nieko nepriklausomas, pasidariau visų vergas, kad tik daugiau jų laimėčiau.
20አይሁድንም እጠቅም ዘንድ ከአይሁድ ጋር እንደ አይሁዳዊ ሆንሁ፤ ከሕግ በታች ያሉትን እጠቅም ዘንድ፥ እኔ ራሴ ከሕግ በታች ሳልሆን፥ ከሕግ በታች ላሉት ከሕግ በታች እንዳለሁ ሆንሁ፤
20Žydams buvau kaip žydas, kad laimėčiau žydus. Tiems, kurie laikosi įstatymo, tapau besilaikančiu įstatymo, kad laimėčiau besilaikančius įstatymo, nors pats nesu jam pavaldus.
21ሕግ የሌላቸውን እጠቅም ዘንድ፥ ያለ እግዚአብሔር ህግ ሳልኖር ነገር ግን በክርስቶስ ሕግ በታች ሳለሁ፥ ሕግ ለሌላቸው ሕግ እንደ ሌለኝ ሆንሁ፤
21Tiems, kurie neturi įstatymo, buvau kaip neturintis įstatymo,­ pats būdamas ne be Dievo įstatymo, bet surištas Kristaus įstatymu,­kad laimėčiau tuos, kurie neturi įstatymo.
22ደካሞችን እጠቅም ዘንድ ለደካሞች እንደ ደካማ ሆንሁ፤ በሁሉ መንገድ አንዳንዶችን አድን ዘንድ፥ ከሁሉ ጋር በሁሉ ነገር እንደ እነርሱ ሆንሁ።
22Silpniesiems pasidariau kaip silpnas, kad laimėčiau silpnuosius. Visiems tapau viskuo, kad vienaip ar kitaip kai kuriuos išgelbėčiau.
23በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።
23Visa tai darau dėl Evangelijos, kad būčiau jos dalininkas.
24በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።
24Argi nežinote, kad lenktynėse bėga visi, bet tik vienas gauna laimėtojo apdovanojimą? Taigi bėkite taip, kad laimėtumėte!
25የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል፤ እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው፥ እኛ ግን የማይጠፋውን።
25Kiekvienas varžybų dalyvis nuo visko susilaiko; jie taip daro, norėdami gauti vystantį vainiką, o mes­nevystantį.
26ስለዚህ እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ አልሮጥም፥ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም፤
26Todėl aš bėgu nedvejodamas ir grumiuosi ne kaip į orą smūgiuodamas,
27ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ።
27bet tramdau savo kūną ir darau jį klusnų, kad, kitiems skelbdamas, pats netapčiau atmestinas.