Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Corinthians

8

1Dėl aukų stabams mums aišku: mes visi turime pažinimą. Pažinimas išpučia, bet meilė ugdo.
1ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋም፥ ሁላችን እውቀት እንዳለን እናውቃለን። እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል።
2Jei kas mano ką nors žinąs, tai jis dar nieko nežino, kaip turi žinoti.
2ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤
3Bet kas myli Dievą, tas yra Jo pažintas.
3ማንም ግን እግዚአብሔርን ቢወድ እርሱ በእርሱ ዘንድ የታወቀ ነው።
4Taigi dėl stabams paaukotų dalykų valgymo mes žinome, kad stabas pasaulyje yra niekas ir kad nėra jokių kitų dievų, kaip tik vienas Dievas.
4እንግዲህ ለጣዖት የተሠዋውን ሥጋ ስለ መብላት፥ ጣዖት ሁሉ በዓለም ከንቱ እንደ ሆነ ከአንዱም በቀር ማንም አምላክ እንደሌለ እናውቃለን።
5Ir nors yra vadinamųjų dievų danguje ar žemėje,­daug tų dievų ir daug viešpačių,­
5መቼም ብዙ አማልክትና ብዙ ጌቶች አሉ፤ ነገር ግን በሰማይ ሆነ በምድርም ሆነ አማልክት የተባሉ ምንም ቢኖሩ፥
6tai mes turime tik vieną Dievą, Tėvą, iš kurio yra visa ir Jam esame mes, ir vieną Viešpatį, Jėzų Kristų, per kurį yra visa ir mes per Jį.
6ለእኛስ ነገር ሁሉ ከእርሱ የሆነ እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ አለን፥ ነገር ሁሉም በእርሱ በኩል የሆነ እኛም በእርሱ በኩል የሆንን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አለን።
7Bet ne visi turi tokį pažinimą. Kai kurie su sąžine, pripažįstančia stabus, iki šiol valgo maistą, kaip stabams paaukotą, ir jų silpna sąžinė susitepa.
7ነገር ግን ይህ እውቀት በሁሉ ዘንድ አይገኝም፤ አንዳንዶች ግን ጣዖትን እስከ አሁን ድረስ ስለ ለመዱ። ለጣዖት የተሠዋ ነው ብለው ይበላሉና ሕሊናቸው ደካማ ስለ ሆነ ይረክሳል።
8Maistas nepriartina mūsų prie Dievo. Kai valgome, nieko nelaimime, ir kai nevalgome, nieko neprarandame.
8መብል ግን ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላም ምንም አይጎድለንም ብንበላም ምንም አይተርፈንም።
9Bet žiūrėkite, kad ši jūsų laisvė netaptų papiktinimu silpniesiems.
9ዳሩ ግን ይህ መብታችሁ ለደካሞች ዕንቅፋት እንዳይሆንባቸው ተጠንቀቁ።
10Antai, jei kas pamatytų tave, turintį pažinimą ir valgantį stabų šventykloje, argi silpno žmogaus sąžinė nebus paskatinta valgyti stabams paaukoto maisto?
10አንተ እውቀት ያለህ በጣዖት ቤት በማዕድ ስትቀመጥ አንድ ሰው ቢያይህ፥ ደካማ ሰው ቢሆን ለጣዖት የተሠዋውን ለመብላት ሕሊናው አይታነጽበትምን?
11Ar dėl tavo pažinimo nežus silpnas brolis, už kurį mirė Kristus?
11በአንተ እውቀትም ይህ ደካማ ይጠፋል፥ እርሱም ክርስቶስ የሞተለት ወንድም ነው።
12Šitaip nusidėdami broliams ir sužeisdami jų silpnas sąžines, nusidedate Kristui.
12እንዲህም ወንድሞችን እየበደላችሁ ደካማም የሆነውን ሕሊናቸውን እያቆሰላችሁ ክርስቶስን ትበድላላችሁ።
13Todėl jei valgis piktina mano brolį, aš nevalgysiu mėsos per amžius, kad nepapiktinčiau savo brolio.
13ስለዚህም መብል ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ፥ ወንድሜን እንዳላሰናክለው ለዘላለም ከቶ ሥጋ አልበላም።