Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Corinthians

4

1Tegul kiekvienas laiko mus Kristaus tarnais ir Dievo paslapčių tvarkytojais.
1እንዲሁ ሰው እኛን እንደ ክርስቶስ ሎሌዎችና እንደ እግዚአብሔር ምሥጢር መጋቢዎች ይቍጠረን።
2O iš tvarkytojų reikalaujama, kad būtų ištikimi.
2እንደዚህም ሲሆን፥ በመጋቢዎች ዘንድ የታመነ ሆኖ መገኘት ይፈለጋል።
3Man mažai rūpi, ką jūs ar žmonių teismas spręstų apie mane. Ir aš pats savęs neteisiu.
3ነገር ግን በእናንተ ዘንድ ወይም በሌላ ሰው ዘንድ ብፈረድ ለእኔ ምንም አይደለም፤ እኔም በራሴ እንኳ አልፈርድም፤
4Nors nematau nieko netinkamo savyje, bet tuo dar nesu išteisintas. Mano teisėjas yra Viešpats.
4በራሴ ላይ ምንም አላውቅምና፥ ነገር ግን በዚህ አልጸድቅም፤ እኔን የሚፈርድ ግን ጌታ ነው።
5Todėl neteiskite nieko prieš laiką, iki ateis Viešpats, kuris nušvies, kas tamsoje paslėpta, ir atskleis širdžių sumanymus. Tada kiekvienam teks pagyrimas iš Dievo.
5ስለዚህም በጨለማ የተሰወረውን ደግሞ ወደ ብርሃን የሚያወጣ የልብንም ምክር የሚገልጥ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ጊዜው ሳይደርስ አንዳች አትፍረዱ፤ በዚያን ጊዜም ለእያንዳንዱ ምስጋናው ከእግዚአብሔር ዘንድ ይሆናል።
6Visa tai, broliai, jūsų labui pritaikiau sau ir Apolui, kad iš mūsų pasimokytumėte negalvoti daugiau negu parašyta ir kad nepasipūstumėte vienas prieš kitą.
6ወንድሞች ሆይ፥ ስለ አንዱ በአንዱ ላይ አንዳችሁም እንዳይታበዩ። ከተጻፈው አትለፍ የሚለውን በእኛ ትማሩ ዘንድ፥ ይህን በእናንተ ምክንያት ስለ ራሴና ስለ አጵሎስ እንደ ምሳሌ ተናገርሁ።
7Kas gi tave išskiria iš kitų? Ir ką gi turi, ko nebūtum gavęs? O jei esi gavęs, tai ko didžiuojies, lyg nebūtum gavęs?
7አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጎሃል? ያልተቀበልኸውስ ምን አለህ? የተቀበልህ ከሆንህ ግን እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለ ምንድር ነው?
8Jūs jau esate sotūs, jau turtingi, jau pradėjote be mūsų karaliauti! O, kad jūs iš tikrųjų karaliautumėte, kad ir mes galėtume kartu karaliauti!
8አሁን ጠግባችኋል፤ አሁንስ ባለ ጠጎች ሆናችኋል፤ ያለ እኛ ነግሣችኋል፤ እኛ ደግሞ ከእናንተ ጋር እንድንነግሥ ብትነግሡ መልካም ይሆን ነበር።
9Man atrodo, kad Dievas mums, apaštalams, paskyrė paskutiniąją vietą, tarsi mirčiai pasmerktiems. Mes tapome reginys pasauliui, angelams ir žmonėms.
9ለዓለም ለመላእክትም ለሰዎችም መጫወቻ ሆነናልና፤ እግዚአብሔር እኛን ሐዋርያቱን ሞት እንደ ተፈረደባቸው ሰዎች ከሁሉ ይልቅ የኋለኞች እንዳደረገን ይመስለኛልና።
10Mes kvaili dėl Kristaus, o jūs išmintingi Kristuje. Mes silpni, o jūs stiprūs; jūs gerbiami, o mes niekinami.
10እኛ ስለ ክርስቶስ ሞኞች ነን እናንተ ግን በክርስቶስ ልባሞች ናችሁ፤ እኛ ደካሞች ነን እናንተ ግን ኃይለኞች ናችሁ፤ እናንተ የከበራችሁ ናችሁ እኛ ግን የተዋረድን ነን።
11Iki šios valandos alkstame ir trokštame, esame nuogi ir mušami, be pastogės
11እስከዚህ ሰዓት ድረስ እንራባለን፥ እንጠማለን፥ እንራቆታለን፥ እንጐሰማለን፥ እንንከራተታለን፥
12ir vargstame, darbuodamiesi savo rankomis. Keikiami­laiminame, persekiojami­kenčiame,
12በገዛ እጃችን እየሠራን እንደክማለን፤ ሲሰድቡን እንመርቃለን፥ ሲያሳድዱን እንታገሣለን፥ ክፉ ሲናገሩን እንማልዳለን፤
13piktžodžiaujami­maloniai atsakome. Iki šiol esame laikomi pasaulio sąšlavomis, visų atmatomis.
13እስከ አሁን ድረስ የዓለም ጥራጊ የሁሉም ጉድፍ ሆነናል።
14Tai rašau, ne norėdamas jus gėdinti, bet įspėdamas kaip mylimus vaikus.
14እንደምወዳችሁ ልጆቼ አድርጌ ልገሥጻችሁ እንጂ ላሳፍራችሁ ይህን አልጽፍም።
15Nors turėtumėte tūkstančius auklėtojų Kristuje, bet neturėsite daug tėvų, nes Evangelija aš pagimdžiau jus Kristuje Jėzuje.
15በክርስቶስ አእላፍ ሞግዚቶች ቢኖሩአችሁ ብዙ አባቶች የሉአችሁም እኔ በክርስቶስ ኢየሱስ በወንጌል ወልጄአችኋለሁና።
16Todėl raginu jus: būkite mano sekėjai!
16እንግዲህ እኔን የምትመስሉ ሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ።
17Tuo tikslu ir pasiunčiau pas jus Timotiejų, kuris yra mano mylimas sūnus ir ištikimas Viešpatyje. Jis jums primins mano kelius Kristuje, kaip aš mokau visur, kiekvienoje bažnyčioje.
17ስለዚህ የምወደውንና የታመነውን በጌታ ልጄ የሆነውን ጢሞቴዎስን ልኬላችኋለሁ፥ እኔም በየስፍራው በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንደማስተምር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚሆነውን መንገዴን እርሱ ያሳስባችኋል።
18Kai kurie pasipūtė, tartum neketinčiau pas jus atvykti.
18አንዳንዱ ግን ወደ እናንተ የማልመጣ እየመሰላቸው የታበዩ አሉ፤
19Jei Viešpats panorės, veikiai atvyksiu pas jus ir patikrinsiu ne pasipūtusių kalbas, bet jėgą.
19ነገር ግን ጌታ ቢፈቅድ ፈጥኜ ወደ እናንተ እመጣለሁ፥ የትዕቢተኞችንም ኃይል አውቃለሁ እንጂ ቃላቸውን አይደለም፤
20Nes Dievo karalystė yra ne kalboje, bet jėgoje.
20የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ነው እንጂ በቃል አይደለምና።
21Ko norite? Ar kad ateičiau pas jus su lazda, ar su meile ir romumo dvasia?
21ምን ትወዳላችሁ? በበትር ወይስ በፍቅርና በየውሃት መንፈስ ልምጣባችሁን?