1Aš, broliai, negalėjau kalbėti jums kaip dvasiniams, bet kaip kūniškiems, kaip kūdikiams Kristuje.
1እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ የሥጋ እንደ መሆናችሁ፥ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም።
2Maitinau jus pienu, ne tvirtu maistu, kurio jūs negalėjote priimti. Net ir dabar negalite,
2ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ፤
3nes tebesate kūniški. Jeigu tarp jūsų pavydas, nesantaika ir susiskaldymai,argi nesate kūniški? Argi nesielgiate grynai žmogiškai?
3ገና ሥጋውያን ናችሁና እስከ አሁን ድረስ ገና አትችሉም። ቅናትና ክርክር ስለሚገኝባችሁ ሥጋውያን መሆናችሁ አይደላችሁምን? እንደ ሰው ልማድስ አትመላለሱምን?
4Kol vienas sako: “AšPauliaus”, kitas: “AšApolo”,argi nesate kūniški?
4አንዱ። እኔ የጳውሎስ ነኝ፥ ሁለተኛውም። እኔ የአጵሎስ ነኝ ቢል ሰዎች ብቻ መሆናችሁ አይደለምን?
5Kas yra Paulius? Kas yra Apolas? Tarnai, kurių dėka įtikėjote ir kurie tarnavo, kiek Viešpats kiekvienam skyrė.
5አጵሎስ እንግዲህ ምንድር ነው? ጳውሎስስ ምንድር ነው? በእነርሱ እጅ ያመናችሁ አገልጋዮች ናቸው፤ ለእያንዳንዳቸውም ጌታ እንደ ሰጣቸው ያገለግላሉ።
6Aš sodinau, Apolas laistė, o Dievas augino.
6እኔ ተከልሁ አጵሎስም አጠጣ ነገር ግን እግዚአብሔር ያሳድግ ነበር፤
7Todėl nieko nereiškia nei sodintojas, nei laistytojas, bet Dievasaugintojas.
7እንግዲያስ የሚያሳድግ እግዚአብሔር እንጂ የሚተክል ቢሆን ወይም የሚያጠጣ ቢሆን አንዳች አይደለም።
8Kas sodina ir kas laisto, yra viena, ir kiekvienas gaus savąjį užmokestį pagal savo triūsą.
8የሚተክልና የሚያጠጣ አንድ ናቸው፥ ነገር ግን እያንዳንዱ እንደ ራሱ ድካም መጠን የራሱን ደመወዝ ይቀበላል።
9Mes juk esame Dievo bendradarbiai, o jūsDievo dirva, Dievo statinys.
9የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንፃ ናችሁ፤ ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና።
10Pagal Dievo man suteiktą malonę aš, kaip išmintingas statybos vadovas, padėjau pamatą, o kitas stato ant jo. Tegul kiekvienas žiūri, kaip stato.
10የእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ተሰጠኝ መጠን እንደ ብልሃተኛ የአናጺ አለቃ መሠረትን መሠረትሁ፥ ሌላውም በላዩ ያንጻል። እያንዳንዱ ግን በእርሱ ላይ እንዴት እንዲያንጽ ይጠንቀቅ።
11Juk niekas negali dėti kito pamato, kaip tik tą, kuris jau padėtas, kuris yra Jėzus Kristus.
11ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
12Jei kas stato ant šio pamato iš aukso, sidabro, brangakmenių, medžio, šieno ar šiaudų,
12ማንም ግን በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ቢሆን በብርም በከበረ ድንጋይም በእንጨትም በሣርም ወይም በአገዳ ቢያንጽ፥ የእያንዳንዱ ሥራ ይገለጣል፤
13kiekvieno darbas išaiškės. Todėl, kad diena jį atskleis, nes tai bus atskleista ugnimi ir ugnis ištirs, koks kieno darbas.
13በእሳት ስለሚገለጥ ያ ቀን ያሳያልና፥ የእያንዳንዱም ሥራ እንዴት መሆኑን እሳቱ ይፈትነዋል።
14Jei kieno statybos darbas išliks, tas gaus užmokestį.
14ማንም በእርሱ ላይ ያነጸው ሥራ ቢጸናለት ደመወዙን ይቀበላል፤
15O kieno darbas sudegs, tas turės nuostolį, bet jis pats bus išgelbėtas, tačiau kaip per ugnį.
15የማንም ሥራ የተቃጠለበት ቢሆን ይጎዳበታል፥ እርሱ ራሱ ግን ይድናል ነገር ግን በእሳት እንደሚድን ይሆናል።
16Ar nežinote, kad jūs esate Dievo šventykla ir Dievo Dvasia gyvena jumyse?
16የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?
17Jei kas Dievo šventyklą niokoja, tą Dievas sunaikins, nes Dievo šventykla šventa, ir toji šventyklatai jūs!
17ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።
18Tegul niekas savęs neapgaudinėja. Jei kas tarp jūsų tariasi esąs išmintingas šiame pasaulyje, tepasidaro kvailas, kad būtų išmintingas.
18ማንም ራሱን አያታልል፤ ከእናንተ ማንም በዚች ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ሞኝ ይሁን።
19Šio pasaulio išmintis Dievo akyse yra kvailystė, nes parašyta: “Jis sugauna protinguosius jų gudrybėje”.
19የዚህች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤ ደግሞም። ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።
20Ir vėl: “Viešpats žino išminčių mintis, kad jos tuščios”.
21ስለዚህም ማንም በሰው አይመካ። ነገር ሁሉ የእናንተ ነውና፤
21Tad niekas tenesididžiuoja žmonėmis! Nes viskas yra jūsų:
22ጳውሎስ ቢሆን አጵሎስም ቢሆን ኬፋም ቢሆን ዓለምም ቢሆን ሕይወትም ቢሆን ሞትም ቢሆን ያለውም ቢሆን የሚመጣውም ቢሆን፥
22ar Paulius, ar Apolas, ar Kefas, ar pasaulis, ar gyvenimas, ar mirtis, ar dabartis, ar ateitis,viskas yra jūsų,
23ሁሉ የእናንተ ነው፥ እናንተም የክርስቶስ ናችሁ ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው።
23bet jūs patysKristaus, o KristusDievo.