1Mano vaikeliai, rašau jums tai, kad nenusidėtumėte. O jei kuris nusidėtų, tai mes turime Užtarėją pas Tėvą, teisųjį Jėzų Kristų.
1ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
2Jis yra permaldavimas už mūsų nuodėmes, ir ne tik už mūsų, bet ir už viso pasaulio.
2እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ።
3Iš to mes patiriame, kad Jį pažįstame, jei laikomės Jo įsakymų.
3ትእዛዛቱንም ብንጠብቅ በዚህ እንዳወቅነው እናውቃለን።
4Kas sako: “Aš Jį pažįstu”, bet Jo įsakymų nesilaiko, tas melagis, ir nėra jame tiesos.
4አውቄዋለሁ የሚል ትእዛዛቱንም የማይጠብቅ ውሸተኛ ነው እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም።
5O kas laikosi Jo žodžių, tame iš tiesų Dievo meilė tobula tapo. Iš to ir pažįstame, jog Jame esame.
5ቃሉን ግን የሚጠብቅ ሁሉ በእርሱ የእግዚአብሔር ፍቅር በእውነት ተፈጽሞአል። በእርሱ እንዳለን በዚህ እናውቃለን፤
6Kas sako esąs Jame, tas turi pats taip elgtis, kaip ir Jis elgėsi.
6በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል።
7Broliai, aš jums nerašau naujo įsakymo, bet seną įsakymą, kurį turėjote nuo pradžios. Senas įsakymas yra žodis, kurį girdėjote nuo pradžios.
7ወንድሞች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረቻችሁ አሮጌ ትእዛዝ እንጂ የምጽፍላችሁ አዲስ ትእዛዝ አይደለችም፤ አሮጌይቱ ትእዛዝ የሰማችኋት ቃል ናት።
8Ir vis dėlto rašau jums naują įsakymą, kuris tikras Jame ir jumyse, nes tamsa traukiasi, o tikroji šviesa jau šviečia.
8ዳግመኛ አዲስ ትእዛዝን እጽፍላችኋለሁ፥ ይህም ነገር በእርሱ በእናንተም እውነተኛ ነው፤ ጨለማው ያልፋልና እውነተኛውም ብርሃን አሁን ይበራል።
9Kas sakosi esąs šviesoje, o savo brolio nekenčia, tas dar tebėra tamsoje.
9በብርሃን አለሁ የሚል ወንድሙንም የሚጠላ እስከ አሁን በጨለማ አለ።
10Kas myli savo brolį, tas pasilieka šviesoje, ir jame nėra nieko piktinančio.
10ወንድሙንም የሚወድ በብርሃን ይኖራል ማሰናከያም የለበትም፤
11O kas savo brolio nekenčia, tas yra tamsoje, vaikščioja tamsoje ir nežino, kur einąs, nes tamsa užgulė jam akis.
11ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል፥ የሚሄድበትንም አያውቅም፥ ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና።
12Rašau jums, vaikeliai, nes dėl Jo vardo atleistos jums nuodėmės.
12ልጆች ሆይ፥ ኃጢአታችሁ ስለ ስሙ ተሰርዮላችኋልና እጽፍላችኋለሁ።
13Rašau jums, tėvai, nes pažinote Tą, kuris yra nuo pradžios. Ir jums, jaunuoliai, rašau, nes nugalėjote piktąjį. Rašau jums, vaikeliai, nes pažinote Tėvą.
13አባቶች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ጎበዞች ሆይ፥ ክፉውን አሸንፋችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ልጆች ሆይ፥ አብን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ።
14Parašiau jums, tėvai, nes pažinote Tą, kuris yra nuo pradžios. Parašiau jums, jaunuoliai, nes jūs stiprūs ir jumyse laikosi Dievo žodis, ir jūs nugalėjote piktąjį.
14አባቶች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ጐበዞች ሆይ፥ ብርቱዎች ስለ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም ቃል በእናንተ ስለሚኖር ክፉውንም ስለ አሸነፋችሁ እጽፍላችኋለሁ።
15Nemylėkite pasaulio, nei to, kas yra pasaulyje. Jei kas myli pasaulį, nėra jame Tėvo meilės,
15ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም።
16nes visa, kas pasaulyje, tai kūno geismas, akių geismas ir gyvenimo išdidumas, o tai nėra iš Tėvo, bet iš pasaulio.
17ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል።
17Praeina pasaulis ir jo geismai, bet kas vykdo Dievo valią, tas išlieka per amžius.
18ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥ የክርስቶስም ተቃዋሚ ይመጣ ዘንድ እንደ ሰማችሁ አሁን እንኳ ብዙዎች የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ተነሥተዋል፤ ስለዚህም መጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ እናውቃለን።
18Vaikeliai, tai paskutinė valanda. Kaip esate girdėję, kad ateis antikristas, tai jau dabar pasirodė daug antikristų. Iš to sprendžiame, jog tai paskutinė valanda.
19ከእኛ ዘንድ ወጡ፥ ዳሩ ግን ከእኛ ወገን አልነበሩም፤ ከእኛ ወገንስ ቢሆኑ ከእኛ ጋር ጸንተው በኖሩ ነበር፤ ነገር ግን ሁሉ ከእኛ ወገን እንዳልሆኑ ይገለጡ ዘንድ ወጡ።
19Jie yra išėję iš mūsų, tačiau nebuvo mūsiškiai. Jeigu jie būtų buvę mūsiškiai, jie būtų likę su mumis. Bet turėjo paaiškėti, jog ne visi yra mūsiškiai.
20እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ።
20Bet jūs turite Šventojo patepimą ir žinote viską.
21እውነትን የምታውቁ ስለ ሆናችሁ፥ ውሸትም ሁሉ ከእውነት እንዳልሆነ ስለምታውቁ እንጂ እውነትን ስለማታውቁ አልጽፍላችሁም።
21Aš parašiau jums ne kaip nežinantiems tiesos, bet todėl, kad pažįstate ją, o iš tiesos negali kilti joks melas.
22ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ውሸተኛው ማን ነው? አብንና ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው።
22Kas yra melagis, jeigu ne tas, kuris neigia, kad Jėzus yra Pateptasis? Tas yra antikristas, kuris neigia Tėvą ir Sūnų.
23ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ እንኳ የለውም፤ በወልድ የሚታመን አብ ደግሞ አለው።
23Kiekvienas, kas neigia Sūnų, neturi ir Tėvo. Kas išpažįsta Sūnų, tas turi ir Tėvą.
24እናንተስ ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ጸንቶ ይኑር። ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ቢኖር፥ እናንተ ደግሞ በወልድና በአብ ትኖራላችሁ።
24Todėl tepasilieka jumyse tai, ką girdėjote nuo pradžios. Jeigu tai, ką girdėjote nuo pradžios, pasilieka jumyse, tada ir jūs pasiliksite Sūnuje ir Tėve.
25እርሱም የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው።
25Štai pažadas, kurį Jis pats mums davė,amžinasis gyvenimas.
26ስለሚያስቱአችሁ ሰዎች ይህን ጽፌላችኋለሁ።
26Aš tai parašiau apie tuos, kurie jus klaidina.
27እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ።
27Bet patepimas, kurį iš Jo gavote, pasilieka jumyse, ir nereikia, kad jus kas nors mokytų, nes pats Jo patepimas moko jus visko, ir jis yra tiesa, o ne melas. Ir kadangi jis jus pamokė, jūs Jame pasiliksite.
28አሁንም፥ ልጆች ሆይ፥ በሚገለጥበት ጊዜ እምነት እንዲሆንልን በመምጣቱም በእርሱ ፊት እንዳናፍር በእርሱ ኑሩ።
28Taigi dabar, vaikeliai, pasilikite Jame, kad, kai Jis pasirodys, turėtumėte pasitikėjimą ir, kai Jis ateis, nebūtume prieš Jį sugėdinti.
29ጻድቅ እንደ ሆነ ካወቃችሁ ጽድቅን የሚያደርግ ሁሉ ከእርሱ እንደ ተወለደ እወቁ።
29Jei žinote, kad Jis teisus, tai žinokite, kad kiekvienas, kuris vykdo teisumą, iš Jo yra gimęs.