Lithuanian

Amharic: New Testament

1 John

3

1Žiūrėkite, kokia meile apdovanojo mus Tėvas: mes vadinamės Dievo vaikai­ir esame! Pasaulis nepažįsta mūsų, nes ir Jo nepažino.
1የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ፥ እንዲሁም ነን። ስለዚህ ምክንያት ዓለም እርሱን ስላላወቀው እኛን አያውቀንም።
2Mylimieji, dabar mes esame Dievo vaikai, bet dar nepasirodė, kas būsime. Mes žinome, kad, kai Jis pasirodys, būsime panašūs į Jį, nes matysime Jį tokį, koks Jis yra.
2ወዳጆች ሆይ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን።
3Kiekvienas, kas turi Jame tokią viltį, skaistina pats save, nes ir Jis yra skaistus.
3በእርሱም ይህን ተስፋ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ንጹሕ እንደ ሆነ ራሱን ያነጻል።
4Kiekvienas, kuris daro nuodėmę, laužo įstatymą. Nuodėmė­ tai įstatymo laužymas.
4ኃጢአትን የሚያደርግ ሁሉ ዓመፅን ደግሞ ያደርጋል፥ ኃጢአትም ዓመፅ ነው።
5Jūs žinote, jog Jis pasirodė, kad sunaikintų mūsų nuodėmes, ir Jame nėra nuodėmės.
5እርሱም ኃጢአትን ሊያስወግድ እንደ ተገለጠ ታውቃላችሁ፥ በእርሱም ኃጢአት የለም።
6Kas pasilieka Jame, tas nenusideda. Kiekvienas nuodėmiaujantis Jo neregėjo ir nepažino.
6በእርሱ የሚኖር ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም፤ ኃጢአትን የሚያደርግ ሁሉ አላየውም አላወቀውምም።
7Vaikeliai! Tegul niekas jūsų nesuklaidina! Vykdantis teisumą yra teisus, kaip ir Jis teisus.
7ልጆች ሆይ፥ ማንም አያስታችሁ፤ እርሱ ጻድቅ እንደ ሆነ ጽድቅን የሚያደርግ ጻድቅ ነው።
8Kas daro nuodėmę, tas iš velnio, nes velnias nuodėmiauja nuo pat pradžios. Todėl ir pasirodė Dievo Sūnus, kad sugriautų velnio darbus.
8ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፥ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና።
9Kas yra gimęs iš Dievo, nedaro nuodėmės, nes jame laikosi Dievo sėkla. Jis negali nuodėmiauti, nes yra gimęs iš Dievo.
9ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም፥ ዘሩ በእርሱ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔርም ተወልዶአልና ኃጢአትን ሊያደርግ አይችልም።
10Taip išaiškėja Dievo vaikai ir velnio vaikai: tas, kuris nevykdo teisumo, nėra iš Dievo; taip pat tas, kuris savo brolio nemyli.
10የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች በዚህ የተገለጡ ናቸው፤ ጽድቅን የማያደርግና ወንድሙን የማይወድ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም።
11Tokia yra žinia, kurią girdėjote nuo pradžios: mes turime mylėti vieni kitus.
11ከመጀመሪያ የሰማችኋት መልእክት። እርስ በርሳችን እንዋደድ የምትል ይህች ናትና፤
12Ne kaip Kainas, kuris buvo iš piktojo ir nužudė savo brolį. Kodėl nužudė? Todėl, kad jo darbai buvo pikti, o brolio­teisūs.
12ከክፉው እንደ ነበረ ወንድሙንም እንደ ገደለ እንደ ቃየል አይደለም፤ ስለ ምንስ ገደለው? የገዛ ሥራው ክፉ፥ የወንድሙም ሥራ ጽድቅ ስለ ነበረ ነው።
13Nesistebėkite, broliai, jei pasaulis jūsų nekenčia.
13ወንድሞች ሆይ፥ ዓለም ቢጠላችሁ አትደነቁ።
14Mes žinome, jog iš mirties perėjome į gyvenimą, nes mylime brolius. Kas nemyli savo brolio, tas pasilieka mirtyje.
14እኛ ወንድሞችን የምንወድ ስለ ሆንን ከሞት ወደ ሕይወት እንደ ተሻገርን እናውቃለን፤ ወንድሙን የማይወድ በሞት ይኖራል።
15Kiekvienas, kas nekenčia savo brolio, yra žmogžudys, o jūs žinote, kad joks žmogžudys neturi amžinojo gyvenimo, jame pasiliekančio.
15ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው፥ ነፍሰ ገዳይም የሆነ ሁሉ የዘላለም ሕይወት በእርሱ እንዳይኖር ታውቃላችሁ።
16Mes iš to pažinome meilę, kad Jis už mus paguldė savo gyvybę. Ir mes turime guldyti savo gyvybę už brolius.
16እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል።
17Bet jei kas turi šio pasaulio turtų ir, matydamas savo brolį stokojantį, užrakina jam savo širdį,­ kaip jame pasiliks Dievo meilė?
17ነገር ግን የዚህ ዓለም ገንዘብ ያለው፥ ወንድሙም የሚያስፈልገው ሲያጣ አይቶ ያልራራለት ማንም ቢሆን፥ የእግዚአብሔር ፍቅር በእርሱ እንዴት ይኖራል?
18Mano vaikeliai, nemylėkime žodžiu ar liežuviu, bet darbu ir tiesa.
18ልጆቼ ሆይ፥ በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት አንዋደድ።
19Tuo mes pažįstame, jog esame iš tiesos, ir Jo akivaizdoje nuraminame savo širdį.
19ልባችንም በእኛ ላይ በሚፈርድበት ሁሉ፥ ከእውነት እንደ ሆንን በዚህ እናውቃለን በፊቱም ልባችንን እናሳርፋለን፥ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና ሁሉንም ያውቃል።
20Jei mūsų širdis mus smerkia, Dievas didesnis už mūsų širdį ir žino viską.
21ወዳጆች ሆይ፥ ልባችንስ ባይፈርድብን በእግዚአብሔር ዘንድ ድፍረት አለን፥
21Mylimieji, jei mūsų širdis mūsų nesmerkia, pasitikime Dievu
22ትእዛዙንም የምንጠብቅና በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን የምናደርግ ስለሆንን የምንለምነውን ሁሉ ከእርሱ እናገኛለን።
22ir gauname iš Jo, ko tik prašome, nes laikomės Jo įsakymų ir darome, kas Jam patinka.
23ትእዛዚቱም ይህች ናት፥ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናምን ዘንድ፥ ትእዛዝንም እንደ ሰጠን እርስ በርሳችን እንዋደድ ዘንድ።
23O štai Jo įsakymas: kad tikėtume Jo Sūnaus Jėzaus Kristaus vardą ir mylėtume vieni kitus, kaip Jo įsakyta.
24ትእዛዙንም የሚጠብቅ በእርሱ ይኖራል እርሱም ይኖርበታል፤ በዚህም በእኛ እንዲኖር ከሰጠን ከመንፈሱ እናውቃለን።
24Kas laikosi Jo įsakymų, pasilieka Jame ir Jis tame. O kad Jis mumyse pasilieka, žinome iš Dvasios, kurią Jis mums davė.