Lithuanian

Amharic: New Testament

1 John

4

1Mylimieji, ne kiekviena dvasia tikėkite, bet ištirkite dvasias, ar jos iš Dievo, nes pasklido pasaulyje daug netikrų pranašų.
1ወዳጆች ሆይ፥ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፥ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደ ሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና።
2Iš to pažinsite Dievo Dvasią: kiekviena dvasia, kuri išpažįsta Jėzų Kristų kūne atėjusį, yra iš Dievo,
2የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥
3ir kiekviena dvasia, kuri neišpažįsta Jėzaus Kristaus kūne atėjusio, nėra iš Dievo. Tokia­iš antikristo, apie kurį girdėjote, kad jis ateisiąs. Jis jau dabar yra pasaulyje.
3ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ።
4Jūs esate iš Dievo, vaikeliai, ir nugalėjote juos, nes Tas, kuris jumyse, didesnis už tą, kuris pasaulyje.
4ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።
5Jie yra iš pasaulio, todėl kalba kaip iš pasaulio, ir pasaulis jų klauso.
5እነርሱ ከዓለም ናቸው፤ ስለዚህ ከዓለም የሆነውን ይናገራሉ ዓለሙም ይሰማቸዋል።
6Mes esame iš Dievo. Kas pažįsta Dievą, tas mūsų klauso, o kas ne iš Dievo­mūsų neklauso. Iš to pažįstame tiesos Dvasią ir klaidos dvasią.
6እኛ ከእግዚአብሔር ነን፤ እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል፤ ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም። የእውነትን መንፈስና የስሕተትን መንፈስ በዚህ እናውቃለን።
7Mylimieji, mylėkime vieni kitus, nes meilė yra iš Dievo. Kiekvienas, kuris myli, yra gimęs iš Dievo ir pažįsta Dievą.
7ወዳጆች ሆይ፥ ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለ ሆነ፥ የሚወደውም ሁሉ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደ እግዚአብሔርንም ስለሚያውቅ፥ እርስ በርሳችን እንዋደድ።
8Kas nemyli, tas nepažįsta Dievo, nes Dievas yra meilė.
8ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና።
9O Dievo meilė pasireiškė mums tuo, jog Dievas atsiuntė į pasaulį savo viengimį Sūnų, kad gyventume per Jį.
9በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና።
10Meilė­ne tai, jog mes pamilome Dievą, bet kad Jis mus pamilo ir atsiuntė savo Sūnų kaip permaldavimą už mūsų nuodėmes.
10ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።
11Mylimieji, jei Dievas mus taip pamilo, tai ir mes turime mylėti vieni kitus.
11ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል።
12Dievo niekas niekada nėra matęs. Jei mylime vieni kitus, Dievas mumyse pasilieka, ir Jo meilė mumyse tobula tampa.
12እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል።
13Iš to pažįstame, kad pasiliekame Jame ir Jis mumyse: Jis davė mums savo Dvasios.
13ከመንፈሱ ስለ ሰጠን፥ በእርሱ እንድንኖር እርሱም በእኛ እንዲኖር በዚህ እናውቃለን።
14Taigi mes matėme ir liudijame, kad Tėvas atsiuntė Sūnų, pasaulio Gelbėtoją.
14እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኃኒት ሊሆን እንደ ላከው እንመሰክራለን።
15Kiekvienas, kas išpažįsta, kad Jėzus yra Dievo Sūnus, Dievas tame ir tas Dieve pasilieka.
15ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።
16Mes pažinome ir įtikėjome meilę, kuria Dievas mus myli. Dievas yra meilė, ir kas pasilieka meilėje, tas pasilieka Dieve, ir Dievas jame.
16እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል አምነንማል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።
17Tuo meilė pasiekia mumyse tobulumą, kad galime turėti drąsų pasitikėjimą teismo dieną, nes koks Jis yra, tokie ir mes esame šiame pasaulyje.
17በፍርድ ቀን ድፍረት ይሆንልን ዘንድ ፍቅር በዚህ ከእኛ ጋር ተፈጽሞአል፤ እርሱ እንዳለ እኛ ደግሞ እንዲሁ በዚህ ዓለም ነንና።
18Meilėje nėra baimės, nes tobula meilė išveja baimę. Baimėje yra kančia, ir kas bijo, tas nėra tobulas meilėje.
18ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም።
19Mes mylime Jį, nes Jis mus pirmas pamilo.
19እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን።
20Jei kas sako: “Aš myliu Dievą”, o savo brolio nekenčia,­tas melagis. Kas nemyli savo brolio, kurį mato, kaip gali mylėti Dievą, kurio nemato?
20ማንም። እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?
21Mes turime tokį Jo įsakymą: kas myli Dievą, turi mylėti ir savo brolį.
21እግዚአብሔርንም የሚወድ ወንድሙን ደግሞ እንዲወድ ይህች ትእዛዝ ከእርሱ አለችን።