1Kiekvienas, kas tiki, jog Jėzus yra Pateptasis, yra gimęs iš Dievo, ir kiekvienas, kuris myli Gimdytoją, myli ir iš Jo gimusį.
1ክርስቶስ ነው ብሎ በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዶአል፥ ወላጁንም የሚወድ ሁሉ ከእርሱ የተወለደውን ደግሞ ይወዳል።
2Iš to pažįstame mylį Dievo vaikus, kad mylime Dievą ir laikomės Jo įsakymų.
2እግዚአብሔርን ስንወድ ትእዛዛቱንም ስናደርግ የእግዚአብሔርን ልጆች እንድንወድ በዚህ እናውቃለን።
3Nes tai yra Dievo meilėJo įsakymus vykdyti. O Jo įsakymai nėra sunkūs.
3ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም።
4Juk, kas tik gimė iš Dievo, nugali pasaulį; ir štai pergalė, nugalinti pasaulįmūsų tikėjimas!
4ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው።
5O kas gi nugali pasaulį, jei ne tas, kuris tiki, kad Jėzus yra Dievo Sūnus?
5ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው?
6Jis yra Tas, kuris atėjo per vandenį ir kraują,Jėzus Kristus; ne vien per vandenį, bet per vandenį ir kraują. Ir Dvasia tai liudija, nes Dvasia yra tiesa.
6በውኃና በደም የመጣ ይህ ነው እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በውኃውና በደሙ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም።
7Mat yra trys liudytojai danguje: Tėvas, Žodis ir Šventoji Dvasia; ir šitie trys yra viena.
7መንፈስም እውነት ነውና የሚመሰክረው መንፈስ ነው።
8Ir yra trys liudytojai žemėje: Dvasia, vanduo ir kraujas; ir šie trys sutaria kaip vienas.
8የሚመሰክሩት መንፈሱና ውኃው ደሙም ሦስት ናቸውና፤ ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ።
9Jeigu priimame žmonių liudijimą, tai Dievo liudijimas didesnis. O Dievo liudijimas toks: Jis paliudijo apie savo Sūnų.
9የሰውን ምስክር ብንቀበል የእግዚአብሔር ምስክር ከእርሱ ይልቅ ይበልጣል፤ ስለ ልጁ የመሰከረው የእግዚአብሔር ምስክር ይህ ነውና።
10Kas tiki Dievo Sūnų, tas turi liudijimą savyje. Kas netiki Dievu, tas Jį melagiu laiko, nes nepatikėjo liudijimu, kuriuo Dievas paliudijo apie savo Sūnų.
10በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን በነፍሱ ምስክር አለው፤ በእግዚአብሔር የማያምን እግዚአብሔር ስለ ልጁ የመሰከረውን ምስክር ስላላመነ ሐሰተኛ አድርጎታል።
11O liudijimas toks: Dievas mums suteikė amžinąjį gyvenimą, ir tas gyvenimas yra Jo Sūnuje.
11እግዚአብሔርም የዘላለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው።
12Kas turi Sūnų, turi gyvenimą. Kas neturi Dievo Sūnaus, tas neturi gyvenimo.
12ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።
13Tai parašiau jums, tikintiems Dievo Sūnaus vardą, kad žinotumėte turį amžinąjį gyvenimą ir kad tikėtumėte Dievo Sūnaus vardą.
13የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ።
14Ir štai kokį pasitikėjimą mes turime Juo: jei ko tik prašome pagal Jo valią, Jis girdi mus.
14በእርሱ ዘንድ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ እንደ ፈቃዱ አንዳች ብንለምን ይሰማናል።
15O jeigu žinome, kad Jis girdi mus, ko tik prašome, tai ir žinome, kad turime tai, ko Jo prašėme.
15የምንለምነውንም ሁሉ እንዲሰማልን ብናውቅ ከእርሱ የለመነውን ልመና እንደ ተቀበልን እናውቃለን።
16Jei kas mato nusidedant savo brolį, tačiau ne iki mirčiai, teprašo, ir Dievas duos jam gyvybę, būtent tiems, kurie nusideda ne iki mirčiai. Yra nuodėmė iki mirčiai, ir aš kalbu ne apie ją, kad būtų prašoma.
16ማንም ወንድሙን ሞት የማይገባውን ኃጢአት ሲያደርግ ቢያየው ይለምን፥ ሞትም የማይገባውን ኃጢአት ላደረጉት ሕይወት ይሰጥለታል። ሞት የሚገባው ኃጢአት አለ፤ ስለዚያ እንዲጠይቅ አልልም።
17Kiekviena neteisybė yra nuodėmė, tačiau esama nuodėmės ne iki mirčiai.
17ዓመፃ ሁሉ ኃጢአት ነው፥ ሞትም የማይገባው ኃጢአት አለ።
18Mes žinome, jog kiekvienas, gimęs iš Dievo, nenusideda. Kas gimęs iš Dievo, saugo save, ir piktasis jo nepaliečia.
18ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን እንዳያደርግ፥ ነገር ግን ከእግዚአብሔር የተወለደው ራሱን እንዲጠብቅ ክፉውም እንዳይነካው እናውቃለን።
19Mes žinome, jog esame iš Dievo, o visas pasaulis yra piktojo.
19ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።
20Ir mes žinome, kad Dievo Sūnus atėjo ir suteikė mums supratimo, kad pažintume Tikrąjį. Ir mes esame TikrajameJo Sūnuje Jėzuje Kristuje. Šis yra tikrasis Dievas ir amžinasis gyvenimas.
20የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።
21Vaikeliai, saugokitės stabų! Amen.
21ልጆች ሆይ፥ ከጣዖታት ራሳችሁን ጠብቁ።