1Paulius, Dievo valia Kristaus Jėzaus apaštalas, ir brolis TimotiejusDievo bažnyčiai Korinte ir visiems šventiesiems, gyvenantiems visoje Achajoje.
1በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ ወንድሙም ጢሞቴዎስ፥ በአካይያ አገር ሁሉ ከሚኖሩ ቅዱሳን ሁሉ ጋር በቆሮንቶስ ላለች ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን፤
2Malonė jums ir ramybė nuo Dievo, mūsų Tėvo, ir Viešpaties Jėzaus Kristaus!
2ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
3Tebūna palaimintas Dievas, mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus Tėvas, gailestingumo Tėvas ir visokios paguodos Dievas,
3የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።
4kuris guodžia mus kiekviename mūsų sielvarte, kad mes galėtume paguosti bet kokio sielvarto ištiktuosius ta paguoda, kuria patys Dievo guodžiami.
4እርሱ በመከራችን ሁሉ ያጽናናናል፥ ስለዚህም እኛ ራሳችን በእግዚአብሔር በምንጽናናበት መጽናናት በመከራ ሁሉ ያሉትን ማጽናናት እንችላለን።
5Kaip gausėja mumyse Kristaus kentėjimai, taip gausėja per Kristų ir mūsų paguoda.
5የክርስቶስ ሥቃይ በእኛ ላይ እንደ በዛ፥ እንዲሁ መጽናናታችን ደግሞ በክርስቶስ በኩል ይበዛልናልና።
6Jeigu patiriam sielvartą, tai jūsų paguodai ir išgelbėjimui, kuris padeda iškęsti tokius pačius kentėjimus, kokius mes kenčiame; o jeigu mes guodžiami, tai jūsų nusiraminimui ir išgelbėjimui.
6ዳሩ ግን መከራ ብንቀበል፥ ስለ መጽናናታችሁና ስለ መዳናችሁ ነው፤ ብንጽናናም፥ እኛ ደግሞ የምንሣቀይበት በዚያ ሥቃይ በመጽናት ስለሚደረግ ስለ መጽናናታችሁ ነው።
7Ir mūsų viltis jumis tvirta, nes žinome, kad, būdami kentėjimų dalininkai, būsite ir paguodos dalininkai.
7ተስፋችንም ስለ እናንተ ጽኑ ነው፤ ሥቃያችንን እንደ ተካፈላችሁ እንዲሁም መጽናናታችንን ደግሞ እንድትካፈሉ እናውቃለንና።
8Mes nenorime, broliai, palikti jus nežinioje apie Azijoje mus ištikusią negandą. Mes buvome prislėgti daugiau nei mūsų jėgos leidžiataip, kad nebesitikėjome išliksią gyvi.
8በእስያ ስለ ደረሰብን መከራችን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ታውቁ ዘንድ እንወዳለንና፤ ስለ ሕይወታችን እንኳ ተስፋ እስክንቆርጥ ድረስ ከዓቅማችን በላይ ያለ ልክ ከብዶብን ነበር፤
9Bet patys savyje patyrėme mirties nuosprendį, kad pasitikėtume ne savimi, o Dievu, kuris prikelia mirusius.
9አዎን፥ ሙታንን በሚያነሣ በእግዚአብሔር እንጂ በራሳችን እንዳንታመን፥ እኛ ራሳችን የሞትን ፍርድ በውስጣችን ሰምተን ነበር።
10Jis išgelbėjo mus iš mirties nasrų ir tebegelbsti. Juo mes pasitikime, kad Jis mus gelbės toliau,
10እርሱም ይህን ከሚያህል ሞት አዳነን፥ ያድነንማል፤ እናንተም ደግሞ ስለ እኛ እየጸለያችሁ አብራችሁ ስትረዱን፥ በብዙ ሰዎች በኩል ስለ ተሰጠን ስለ ጸጋ ስጦታ ብዙዎች ስለ እኛ ያመሰግኑ ዘንድ፥ ወደ ፊት ደግሞ እንዲያድን በእርሱ ተስፋ አድርገናል።
11jums padedant malda už mus, kad daugelis dėl mūsų dėkotų už dovaną, per daugelį suteiktą mums.
12ትምክህታችን ይህ ነውና፤ በእግዚአብሔር ጸጋ እንጂ በሥጋዊ ጥበብ ሳይሆን፥ በእግዚአብሔር ቅድስናና ቅንነት በዚህ ዓለም ይልቁንም በእናንተ ዘንድ እንደኖርን የሕሊናችን ምስክርነት ነው።
12Nes mūsų pasigyrimas yra toks: liudija mūsų sąžinė, kad pasaulyje, o ypač pas jus, mes elgėmės paprastai ir su dievišku nuoširdumu,ne kūniška išmintimi, bet Dievo malone.
13ከምታነቡትና ከምታስተውሉት በቀር ሌላ አንጽፍላችሁምና፤ በጌታችን በኢየሱስ ቀን እናንተ ደግሞ ትምክህታችን እንደምትሆኑ እንዲሁ ትምክህታችሁ እንድንሆን፥ በከፊል ስለ እኛ እንዳስተዋላችሁ ፈጽማችሁ ታስተውሉት ዘንድ ተስፋ አደርጋለሁ።
13Nerašome jums nieko kito, kaip tik tai, ką jūs skaitote ir suprantate. Tikiuosi, kad ir iki galo suprasite,
15በዚህም ታምኜ፥ ሁለተኛ ጸጋ ታገኙ ዘንድ አስቀድሜ ወደ እናንተ እንድመጣ፥
14kaip iš dalies jau mus supratote, kad mes esame jūsų pasigyrimas, kaip ir jūs mūsųViešpaties Jėzaus dieną.
16በእናንተም መካከል ወደ መቄዶንያ እንዳልፍ ደግሞም ከመቄዶንያ ወደ እናንተ መጥቼ ወደ ይሁዳ በጉዞዬ እንድትረዱኝ አሰብሁ።
15Tokio pasitikėjimo kupinas, aš norėjau anksčiau pas jus atvykti, kad antrąkart gautumėt malonę,
17እንግዲህ ይህን ሳስብ ያን ጊዜ ቅሌትን አሳየሁን? ወይስ በእኔ ዘንድ አዎን አዎን አይደለም አይደለም ማለት እንዲሆን ያን የማስበው በዓለማዊ ልማድ ነውን?
16ir pro jus keliauti į Makedoniją, o iš Makedonijos vėl grįžti pas jus, kad jūs mane išlydėtumėte į Judėją.
18እግዚአብሔር ግን የታመነ ነው፥ ለእናንተም የሚነገረው ቃላችን አዎንና አይደለም አይሆንም።
17Ar taip manydamas, elgiausi lengvabūdiškai? O gal mano sumanymai buvo pagal kūną, kad mano “taip, taip” yra ir “ne, ne”?
19በእኛ ማለት በእኔና በስልዋኖስ በጢሞቴዎስም በመካከላችሁ የተሰበከ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ አዎንና አይደለም አልነበረም፥ ነገር ግን በእርሱ አዎን ሆኖአል።
18Bet kaip Dievas ištikimas, mūsų žodis jums nebuvo “taip” ir “ne”.
20እግዚአብሔር ለሰጠው የተስፋ ቃል ሁሉ አዎን ማለት በእርሱ ነውና፥ ስለዚህ ለእግዚአብሔር ስለ ክብሩ በእኛ የሚነገረው አሜን በእርሱ ደግሞ ነው።
19Nes Dievo Sūnus, Jėzus Kristus, kurį jums paskelbėme aš, Silvanas ir Timotiejus, nebuvo “taip” ir “ne”, bet Jame buvo “taip”.
21በክርስቶስም ከእናንተ ጋር የሚያጸናንና የቀባን እግዚአብሔር ነው፥
20Nes visi Dievo pažadai Jame yra “taip” ir Jame “amen” Dievo šlovei per mus.
22ደግሞም ያተመን የመንፈሱንም መያዣ በልባችን የሰጠን እርሱ ነው።
21Tas, kuris sutvirtina mus su jumis Kristuje ir mus patepė, yra Dievas,
23እኔ ግን ልራራላችሁ ስል እንደ ገና ወደ ቆሮንቶስ እንዳልመጣሁ በነፍሴ ላይ እግዚአብሔርን ምስክር እጠራለሁ።
22kuris ir užantspaudavo mus ir davė kaip užstatą Dvasią į mūsų širdis.
24ለደስታችሁ ከእናንተ ጋር የምንሠራ ነን እንጂ፥ በእምነታችሁ በእናንተ ላይ የምንገዛ አይደለንም። በእምነታችሁ ቆማችኋልና።
23Šaukiuosi Dievą liudytoju savo sielai, kad jūsų gailėdamas aš neatvykau į Korintą.
24Mes juk neviešpataujame jūsų tikėjimui, bet esame jūsų džiaugsmo talkininkai, nes tikėjimu jūs stovite tvirtai.