1Taigi aš nusprendžiau, kad neatvyksiu pas jus vėl su liūdesiu.
1ነገር ግን ዳግመኛ በኀዘን ወደ እናንተ እንዳልመጣ ስለ እኔ ቆረጥሁ።
2O jei aš jus liūdinu, tai kas gi mane pralinksmins, jeigu ne mano nuliūdintasis?
2እኔስ ባሳዝናችሁ፥ እንግዲያስ በእኔ ምክንያት ከሚያዝን በቀር ደስ የሚያሰኘኝ ማን ነው?
3Aš tai parašiau, kad atvykęs neturėčiau liūdėti dėl tų, kuriais derėtų džiaugtis, pasitikėdamas jumis visais, kad mano džiaugsmas yra ir visų jūsų džiaugsmas.
3ደስ ሊያሰኙኝ ከሚገባቸውም በመምጣቴ ኀዘን እንዳይሆንብኝ ይህንኑ ጻፍሁላችሁ፥ ደስታዬ የሁላችሁ ደስታ ነው ብዬ በሁላችሁ ታምኜአለሁና።
4Nes aš jums rašiau iš didelio skausmo ir širdies sielvarto, su gausiomis ašaromis, ne tam, kad jus nuliūdinčiau, bet kad pažintumėte meilę, kurios taip apsčiai jums turiu.
4በብዙ መከራና ከልብ ጭንቀት በብዙም እንባ ጽፌላችሁ ነበርና፤ ይህም እናንተን አብዝቼ የምወድበትን ፍቅር እንድታውቁ እንጂ እንዳሳዝናችሁ አይደለም።
5Bet jeigu kas nuliūdino, tai nuliūdino ne mane, bet,—kad neperdėčiau,—bent iš daliesjus visus.
5ነገር ግን ማንም አሳዝኖ ቢሆን፥ እንዳልከብድባችሁ፥ በክፍል ሁላችሁን እንጂ እኔን ያሳዘነ አይደለም።
6Tokiam žmogui pakanka daugumos paskirtos bausmės.
6እንደዚህ ላለ ሰው ይህ ከእናንተ የምትበዙት የቀጣችሁት ቅጣት ይበቃዋልና እንደዚህ ያለው ከልክ በሚበዛ ኀዘን እንዳይዋጥ፥
7Net atvirkščiai, jūs turėtumėte jam atleisti ir jį paguosti, kad jo neapimtų pernelyg didelis liūdesys.
7ይልቅ ተመልሳችሁ ይቅር ማለትና ማጽናናት ይገባችኋል።
8Todėl aš prašau jus parodyti jam meilę.
8ስለዚህ ከእርሱ ጋር ፍቅርን እንድታጸኑ እለምናችኋለሁ፤
9Nes tuo tikslu jums ir parašiau, kad patikrinčiau, ar jūs visais atžvilgiais esate klusnūs.
9ስለዚህ ደግሞ ጽፌ ነበርና፤ በሁሉ የምትታዘዙ እንደ ሆናችሁ የእናንተን መፈተን አውቅ ዘንድ አሳቤ ነበር።
10Kam jūs atleidžiate, tam atleidžiu ir aš; nes, jei kam atleidau, tai padariau dėl jūsų Kristaus akivaizdoje,
10እናንተ ግን ይቅር የምትሉትን እኔ ደግሞ ይቅር እለዋለሁ፤ እኔም ይቅር ካልሁ፥ ይቅር ያልሁትን ስለ እናንተ በክርስቶስ ፊት ይቅር ብዬአለሁ፥
11kad neapgautų mūsų šėtonas. Nes mums nėra nežinomi jo kėslai.
11በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና።
12Kai atvykau į Troadę skelbti Kristaus Evangelijos, durys man buvo Viešpaties atvertos,
12ስለ ክርስቶስም ወንጌል ወደ ጢሮአዳ በመጣሁ ጊዜ፥ ለጌታ ሥራ በር ምንም ቢከፈትልኝ፥ ቲቶን ወንድሜን ስላላገኘሁት መንፈሴ ዕረፍት አልነበረውም፥
13bet aš neturėjau savo dvasioje ramybės, kadangi nesutikau savo brolio Tito; tad atsisveikinęs iškeliavau į Makedoniją.
13ነገር ግን ከእነርሱ ተሰናብቼ ወደ መቄዶንያ ወጣሁ።
14Dėkui Dievui, kuris visada veda mus Kristuje triumfo eisenoje ir per mus kiekvienoje vietoje skleidžia mielą Jo pažinimo kvapą.
14ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤
15Juk mes esame Kristaus malonus kvapas Dievui tarp išgelbėtų ir tarp žūstančių.
15በሚድኑቱና በሚጠፉቱ ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና፤
16Vieniemsmirties kvapas mirčiai, kitiemsgyvenimo kvapas gyvenimui. O kas gi yra tam tinkamas?
16ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው?
17Mes neprekiaujame, kaip daugelis, Dievo žodžiu, bet nuoširdžiai, kaip iš Dievo, kalbame Kristuje, Dievo akivaizdoje.
17የእግዚአብሔርን ቃል ቀላቅለው እንደሚሸቃቅጡት እንደ ብዙዎቹ አይደለንምና፤ በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ ተላክን በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።