1Ar pradėsime iš naujo jums prisistatinėti? Gal mums reikia, kaip kai kuriems, palydimųjų laiškų jums ir iš jūsų?
1እንደ ገና ራሳችንን ልናመሰግን እንጀምራለንን? ወይስ እንደ ሌሎች የማመስገኛ መልእክት ወደ እናንተ ወይስ ከእናንተ ያስፈልገን ይሆንን?
2Jūs esate mūsų laiškas, įrašytas mūsų širdyse, visų žmonių suprantamas ir skaitomas.
2ሰዎች ሁሉ የሚያውቁትና የሚያነቡት በልባችን የተጻፈ መልእክታችን እናንተ ናችሁ።
3Jūs pasirodote esą Kristaus laiškas, mūsų tarnavimu parašytas ne rašalu, bet gyvojo Dievo Dvasia, ne akmens plokštėse, bet gyvų širdžių plokštėse.
3እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም አይደለም፥ ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት እንጂ በድንጋይ ጽላት ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው።
4Tokį pasitikėjimą Dievu mes turime per Kristų.
4በክርስቶስም በኩል ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ያለ እምነት አለን።
5Ne todėl, kad būtume patys tinkami ką nors sumanyti tarytum iš savęs, bet mūsų tinkamumas iš Dievo,
5ብቃታችን ከእግዚአብሔር ነው እንጂ፥ በገዛ እጃችን እንደሚሆን አንዳችን እንኳ ልናስብ ራሳችን የበቃን አይደለንም፤
6kuris padarė mus tinkamus būti Naujosios Sandoros tarnaisne raidės, bet Dvasios, nes raidė žudo, o Dvasia teikia gyvybę.
6እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን ዘንድ አበቃን፤ ፊደል ይገድላልና መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል።
7Jeigu mirties tarnavimas, išraižytas raidėmis akmenyse, buvo toks šlovingas, kad Izraelio vaikai negalėjo pažvelgti Mozei į veidą dėl jo veido šlovės, kuri buvo praeinanti,
7ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ ስለ ተሻረው ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት በክብር ከሆነ፥
8tai kiek šlovingesnis bus Dvasios tarnavimas?
8የመንፈስ አገልግሎት እንዴት ይልቅ በክብር አይሆንም?
9Jeigu pasmerkimo tarnavimas šlovingas, tai daug daugiau šlovingesnis teisumo tarnavimas.
9የኵነኔ አገልግሎት ክብር ከሆነ፥ ይልቅ የጽድቅ አገልግሎት በክብር አብዝቶ ይበልጣልና።
10Tai, kas buvo šlovinga, visai nešlovinga, lyginant su visa pranokstančia šlove.
10ያ የከበረ እንኳ እጅግ በሚበልጠው ክብር ምክንያት በዚህ ነገር ክብሩን አጥቶአልና።
11Jeigu praeinantis dalykas buvo šlovingas, tai kur kas šlovingesnis pasiliekantis.
11ያ ይሻር የነበረው በክብር ከሆነ፥ ጸንቶ የሚኖረውማ እጅግ ይልቅ በክብር ሆኖአልና።
12Taigi, turėdami tokią viltį, mes kalbame labai tiesiai ir drąsiai,
12እንግዲህ እንዲህ ያለ ተስፋ ካለን እጅግ ገልጠን እንናገራለን፥
13ne kaip Mozė, kuris ant veido užsileisdavo gaubtuvą, kad Izraelio vaikai nepamatytų to, kas praeina.
13የዚያንም ይሻር የነበረውን መጨረሻ ትኵር ብለው የእስራኤል ልጆች እንዳይመለከቱ፥ በፊቱ መጋረጃ እንዳደረገ እንደ ሙሴ አይደለንም።
14Bet jų protai buvo apakinti. Iki šios dienos tas pats gaubtuvas lieka nenuimtas skaitant Senąjį Testamentą, nes jis nuimamas Kristuje.
14ነገር ግን አሳባቸው ደነዘዘ። ብሉይ ኪዳን ሲነበብ ያ መጋረጃ ሳይወሰድ እስከ ዛሬ ድረስ ይኖራልና፤ በክርስቶስ ብቻ የተሻረ ነውና።
15Net iki šios dienos, kai skaitomas Mozė, gaubtuvas tebedengia jų širdį.
15ነገር ግን እስከ ዛሬ ድረስ የሙሴ መጻሕፍት በተነበቡ ጊዜ ሁሉ ያ መጋረጃ በልባቸው ይኖራል፤
16Bet kai žmogus atsigręžia į Viešpatį, gaubtuvas nuimamas.
16ወደ ጌታ ግን ዘወር ባለ ጊዜ ሁሉ መጋረጃው ይወሰዳል።
17Viešpats yra Dvasia. O kur Viešpaties Dvasia, ten laisvė.
17ጌታ ግን መንፈስ ነው፤ የጌታም መንፈስ ባለበት በዚያ አርነት አለ።
18Mes visi, atidengtu veidu lyg veidrodyje regėdami Viešpaties šlovę, esame keičiami į tą patį atvaizdą iš šlovės į šlovę, veikiami Viešpaties, kuris yra Dvasia.
18እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።