Lithuanian

Amharic: New Testament

2 Corinthians

11

1O, kad jūs pakęstumėte truputėlį mano kvailumo! Betgi jūs ir pakenčiate.
1በጥቂቱ ሞኝነቴ ብትታገሡኝ መልካም ይሆን ነበር፤ ቢሆንም በእርግጥ ታገሡኝ።
2Aš pavyduliauju dėl jūsų Dievo pavydu, nes sužiedavau jus su vienu vyru, kad nuvesčiau jus Kristui kaip skaisčią mergelę.
2በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤
3Bet bijau, kad kaip gyvatė savo gudrumu suvedžiojo Ievą, taip ir jūsų mintys nesugestų be paprastumo Kristuje.
3ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ።
4Mat jei kas užklydęs ima skelbti kitą Jėzų, kurio mes neskelbėme, arba jei jūs priimate kitą dvasią, kurios nebuvote priėmę, ar kitą evangeliją, kurios nebuvote gavę, jūs ramiausiai tai pakenčiate.
4የሚመጣውም ያልሰበክነውን ሌላ ኢየሱስ ቢሰብክ፥ ወይም ያላገኛችሁትን ልዩ መንፈስ ወይም ያልተቀበላችሁትን ልዩ ወንጌል ብታገኙ፥ በመልካም ትታገሡታላችሁ።
5Bet aš manau nesąs prastesnis už pačius didžiausius apaštalus.
5ከእነዚህ ከዋነኞቹ ሐዋርያት በአንድ ነገር እንኳ እንደ ጎደልሁ ራሴን አልቆጥርም።
6Ir jei man trūksta iškalbingumo, tai anaiptol ne pažinimo. Ir tai jums esame aiškiai įrodę visais atžvilgiais.
6በአነጋገሬ ያልተማርሁ ብሆን እንኳ፥ በእውቀት ግን እንዲህ አይደለሁም። ነገር ግን በሰው ሁሉ መካከል በነገር ሁሉ ተገልጠንላችኋል።
7Nejaugi nusidėjau, kad pažeminau save ir išaukštinau jus, paskelbdamas jums Dievo Evangeliją už dyką?
7ወይስ የእግዚአብሔርን ወንጌል ያለ ደመወዝ ስለ ሰበክሁላችሁ፥ እናንተ ከፍ እንድትሉ ራሴን እያዋረድሁ ኃጢአት አድርጌ ይሆንን?
8Apiplėšiau kitas bažnyčias, imdamas iš jų atlyginimą, kad galėčiau tarnauti jums.
8እናንተን ለማገልገል ደመወዝ እየተቀበልሁ ሌሎችን አብያተ ክርስቲያናት ዘረፍሁ።
9O būdamas pas jus ir stokodamas, nė vieno neapsunkinau, nes ko man trūko, parūpino iš Makedonijos atvykę broliai. Aš saugojausi ir ateityje saugosiuos tapti jums našta bet kuria prasme.
9ከእናንተም ጋር ሳለሁ በጎደለኝ ጊዜ፥ በማንም አልከበድሁበትም፤ ከመቄዶንያ የመጡት ወንድሞች የጎደለኝን በሙሉ ሰጥተዋልና፤ በነገርም ሁሉ እንዳልከብድባችሁ ተጠነቀቅሁ እጠነቀቅማለሁ።
10Sakau jums vardan Kristaus tiesos, esančios manyje, kad šio pasididžiavimo Achajos srityse niekas iš manęs neatims.
10የክርስቶስ እውነት በእኔ እንዳለ፥ ይህ ትምክህት በእኔ ዘንድ በአካይያ አገር አይከለከልም።
11Kodėl? Ar todėl, kad jūsų nemyliu? Dievas žino!
11ስለ ምን? ስለማልወዳችሁ ነውን? እግዚአብሔር ያውቃል።
12Ką darau, darysiu ir toliau, kad negalėtų pasiteisinti norintys pasiteisinti, kad tuo, kuo giriasi, jie pasirodytų esą tokie kaip ir mes.
12ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ ምክንያትን ከሚፈልጉቱ ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።
13Juk tokie yra netikri apaštalai, apgaulingi darbininkai, besidedantys Kristaus apaštalais.
13እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና።
14Ir nenuostabu. Juk pats šėtonas apsimeta šviesos angelu.
14ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።
15Tad nieko ypatingo, jei jo tarnai apsimeta teisumo tarnais. Bet jų galas bus pagal jų darbus.
15እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜአቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል።
16Kartoju: tegu nei vienas nelaiko manęs kvailiu! O jeigu jau laikote, tai pasiklausykite manęs kaip kvailo, kad irgi galėčiau truputį pasigirti.
16እንደ ገና እላለሁ። ለማንም ሰው ሞኝ የሆንሁ አይምሰለው፤ ያለዚያ ግን እኔ ደግሞ ጥቂት እመካ ዘንድ እንደ ሞኝ እንኳ ሆኜ ተቀበሉኝ።
17Ką pasakysiu, pasakysiu ne pagal Viešpatį, bet tarytum kvailiodamas ir manydamas galįs pasigirti.
17እንደዚህ ታምኜ ስመካ የምናገረው፥ በሞኝነት እንጂ ጌታ እንዳዘዘኝ አልናገርም።
18Matydamas, kad daug kas giriasi pagal kūną, tai pasigirsiu ir aš.
18ብዙዎች በዓለማዊ ነገር ስለሚመኩ እኔ ደግሞ እመካለሁ።
19Juk, būdami protingi, mokate mielai pakęsti kvailius.
19ልባሞች ስለምትሆኑ በደስታ ሞኞችን ትታገሣላችሁና፤
20Nes jūs pakenčiate, kai jus pavergia, kai apryja, kai atima, kai didžiuojasi, kai smogia per veidą.
20ማንም ባሪያዎች ቢያደርጋችሁ፥ ማንም ቢበላችሁ፥ ማንም ቢቀማችሁ፥ ማንም ቢኮራባችሁ፥ ማንም ፊታችሁን በጥፊ ቢመታችሁ ትታገሣላችሁና።
21Mūsų gėdai pasakysiu, kad buvome tam per silpni. Bet jei kas kuo nors drąsus,­tai sakau iš kvailumo,­ aš drąsus taip pat.
21ደካሞች መስለን እንደ ነበርን በውርደት እላለሁ። ነገር ግን በሞኝነት እላለሁ፤ ማንም በሚደፍርበት እኔ ደግሞ እደፍርበታለሁ።
22Jie žydai? Ir aš. Jie izraelitai? Ir aš. Jie Abraomo palikuonys? Ir aš.
22ዕብራውያን ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የእስራኤል ወገን ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የአብርሃም ዘር ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የክርስቶስ አገልጋዮች ናቸውን?
23Jie Kristaus tarnai? Kalbu kaip kvailys: aš juo labiau! Aš daug daugiau darbavausi, gavau rykščių be saiko, daugiau kalėjau ir daugel kartų buvau mirties pavojuje.
23እንደ እብድ ሰው እላለሁ፤ እኔ እበልጣለሁ፤ በድካም አብዝቼ፥ በመገረፍ አብዝቼ፥ በመታሰር አትርፌ፥ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ።
24Nuo žydų gavau penkis kartus po keturiasdešimt be vieno kirčio.
24አይሁድ አንድ ሲጎድል አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ ገረፉኝ።
25Tris kartus buvau muštas lazdomis, vienąkart buvau užmėtytas akmenimis. Tris kartus pergyvenau laivo sudužimą, ištisą parą plūduriavau jūroje.
25ሦስት ጊዜ በበትር ተመታሁ፤ አንድ ጊዜ በድንጋይ ተወገርሁ፤ መርከቤ ሦስት ጊዜ ተሰበረ፤ ሌሊትና ቀን በባሕር ውስጥ ኖርሁ።
26Dažnai buvau kelionėse, upių pavojuose, pavojuose nuo plėšikų, pavojuose nuo tautiečių, pavojuose nuo pagonių, pavojuose mieste, dykumos pavojuose, pavojuose jūroje, pavojuose nuo netikrų brolių.
26ብዙ ጊዜ በመንገድ ሄድሁ፤ በወንዝ ፍርሃት፥ በወንበዴዎች ፍርሃት፥ በወገኔ በኩል ፍርሃት፥ በአሕዛብ በኩል ፍርሃት፥ በከተማ ፍርሃት፥ በምድረ በዳ ፍርሃት፥ በባሕር ፍርሃት፥ በውሸተኞች ወንድሞች በኩል ፍርሃት ነበረብኝ፤
27Kenčiau nuovargį ir skausmą, dažnai budėjau naktimis, alkau ir troškau, dažnai pasninkavau, kenčiau šaltį ir nuogumą.
27በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት፥ በራብና በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም፥ በብርድና በራቁትነት ነበርሁ።
28Neminint viso kito, kas atsitinka kasdien, rūpinuosi visomis bažnyčiomis.
28የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።
29Jei kas silpsta, ar aš nesilpstu? Jei kas piktinasi, ar aš nedegu apmaudu?
29የሚደክም ማን ነው፥ እኔም አልደክምምን? የሚሰናከል ማን ነው፥ እኔም አልናደድምን?
30Jei reikia girtis, girsiuosi savo silpnumu.
30ትምክህት የሚያስፈልግ ከሆነ፥ ከድካሜ በሚሆነው ነገር እመካለሁ።
31Dievas, mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus Tėvas, kuris palaimintas per amžius, žino, kad nemeluoju.
31ለዘላለም የተባረከ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት እንዳልዋሽ ያውቃል።
32Damaske karaliaus Areto valdytojas saugojo damaskiečių miestą, norėdamas mane suimti,
32በደማስቆ አርስጦስዮስ ከተባለ ንጉሥ በታች የሆነ የሕዝብ ገዥ ሊይዘኝ እየወደደ የደማስቆ ሰዎችን ከተማ ያስጠብቅ ነበር፥
33bet buvau pro langą nuleistas pintinėje per sieną ir taip ištrūkau iš jo rankų.
33በቅጥሩም ባለ መስኮት በቅርጫት አወረዱኝና ከእጁ አመለጥሁ።