Lithuanian

Amharic: New Testament

2 Corinthians

12

1Jei reikia girtis (nors iš to jokios naudos), eisiu prie Viešpaties regėjimų ir apreiškimų.
1ትምክህት የሚያስፈልግ ነው፤ አይጠቅምም ነገር ግን ከጌታ ወዳለው ራእይና መገለጥ እመጣለሁ።
2Pažįstu žmogų Kristuje, kuris prieš keturiolika metų,­ar kūne, ar be kūno­nežinau, Dievas žino,­buvo paimtas iki trečiojo dangaus.
2ሰውን በክርስቶስ አውቃለሁ፥ በሥጋ እንደ ሆነ አላውቅም ወይም ከሥጋ ውጭ እንደ ሆነ አላውቅም፥ እግዚአብሔር ያውቃል፤ እንዲህ ያለው ሰው ከአሥራ አራት ዓመት በፊት እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ ተነጠቀ።
3Ir žinau, kad šitas žmogus,­ar kūne, ar be kūno­nežinau, Dievas žino,­
3እንዲህ ያለውንም ሰው አውቃለሁ፥ በሥጋ እንደ ሆነ ወይም ያለ ሥጋ እንደ ሆነ አላውቅም፥ እግዚአብሔር ያውቃል፤
4buvo paimtas į rojų ir girdėjo neišreiškiamus žodžius, kurių nevalia žmogui ištarti.
4ወደ ገነት ተነጠቀ፥ ሰውም ሊናገር የማይገባውን የማይነገረውን ቃል ሰማ።
5Tokiu pasigirsiu, o ne savimi, nebent savo negaliomis.
5እንደዚህ ስላለው እመካለሁ፥ ስለ ራሴ ግን ከድካሜ በቀር አልመካም።
6Jei norėčiau girtis, nebūčiau kvailys, nes kalbėčiau tiesą. Bet susilaikau, kad kas nors apie mane nepagalvotų daugiau negu tai, ką manyje mato ar iš manęs girdi.
6ልመካ ብወድስ ሞኝ አልሆንም፥ እውነትን እላለሁና፤ ነገር ግን ማንም ከሚያይ ከእኔም ከሚሰማ የምበልጥ አድርጎ እንዳይቆጥረኝ ትቼአለሁ።
7Ir kad perdėm neišpuikčiau dėl gausybės apreiškimų, man duotas dyglys kūne, šėtono pasiuntinys, kad mane smūgiuotų ir aš neišpuikčiau.
7ስለዚህም በመገለጥ ታላቅነት እንዳልታበይ የሥጋዬ መውጊያ፥ እርሱም የሚጎስመኝ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ፤ ይኸውም እንዳልታበይ ነው።
8Dėl to tris kartus meldžiau Viešpatį, kad tai nuo manęs atitrauktų.
8ስለዚህ ነገር ከእኔ እንዲለይ ሦስት ጊዜ ጌታን ለመንሁ።
9Bet Viešpats man pasakė: “Pakanka tau mano malonės, nes mano stiprybė tampa tobula silpnume”. Todėl mieliausiai girsiuosi savo silpnumais, kad Kristaus jėga ilsėtųsi ant manęs.
9እርሱም። ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ።
10Patenkintas tad silpnumu, paniekinimais, sunkumais, persekiojimais ir priespauda dėl Kristaus, nes, būdamas silpnas, esu galingas.
10ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና።
11Jūsų verčiamas, tapau kvailiu besigirdamas. Iš tikro tai jūs turėtumėte mane girti, nes aš ne prastesnis už pačius didžiausius apaštalus, nors esu niekas.
11በመመካቴ ሞኝ ሆኜአለሁ፤ እናንተ ግድ አላችሁኝ፤ እናንተ እኔን ልታመሰግኑ ይገባ ነበርና። እኔ ምንም ባልሆን እንኳ፥ ከዋነኞቹ ሐዋርያት በምንም አልጎድልምና።
12Iš tiesų jūsų akyse pasitvirtino apaštalo ženklai: visokeriopa kantrybė, ženklai, stebuklai ir galingi darbai.
12በእርግጥ የሐዋርያነት ምልክት በመካከላችሁ በምልክትና በድንቅ ነገር በተአምራትም በሁሉ ትዕግሥት ተደረገ።
13Tad ko jums trūksta palyginti su kitomis bažnyčiomis? Vien to, kad nebuvau jums našta. Atleiskite man šitą nusikaltimą!
13እኔ ራሴ ካልከበድሁባችሁ ከዚህ በቀር፥ ከሌላ ቤተ ክርስቲያን ያነሳችሁበት በምን እኮ ነው? ይህን በደሌን ይቅር በሉልኝ።
14Esu pasiruošęs trečią kartą atvykti pas jus, tačiau neapsunkinsiu jūsų. Ieškau ne to, kas jūsų, bet jūsų pačių. Juk ne vaikai privalo krauti turtą tėvams, bet tėvai vaikams.
14እነሆ፥ ወደ እናንተ እመጣ ዘንድ ስዘጋጅ ይህ ሦስተኛዬ ነው፤ አልከብድባችሁምም፥ እናንተን እንጂ ያላችሁን አልፈልግምና። ወላጆች ለልጆች እንጂ ልጆች ለወላጆች ገንዘብ ሊያከማቹ አይገባቸውምና።
15Todėl mielai išleisiu tai, kas mano, ir dar save pridėsiu jūsų sielų labui; nors, kuo daugiau jus myliu, tuo mažiau esu mylimas.
15እኔ ግን ስለ ነፍሳችሁ በብዙ ደስታ ገንዘቤን እከፍላለሁ፥ ራሴን እንኳ እከፍላለሁ። ከመጠን ይልቅ ብወዳችሁ በዚህ ልክ ፍቅራችሁ የሚያንስ ነውን?
16Tebūnie ir taip,­sakysite,­aš jūsų neapsunkinau, bet, būdamas gudrus, klasta jus pagavau.
16ይሁን እንጂ እኔ አልከበድሁባችሁም፤ ነገር ግን ሸንጋይ ሆኜ በተንኰል ያዝኋችሁ።
17Bet ar kaip nors išnaudojau jus per kurį savo pasiuntinį?
17ወደ እናንተ ከላክኋቸው በአንዱ ስንኳ አታለልኋችሁን?
18Paprašiau Titą keliauti ir pasiunčiau su juo vieną brolį. Ar Titas jus išnaudojo? Ar mes veikėme ne ta pačia dvasia? Ar nevaikščiojome tomis pačiomis pėdomis?
18ቲቶን መከርሁት ከእርሱም ጋር ወንድሙን ላክሁት፤ ቲቶስ አታለላችሁን? በአንድ መንፈስ አልተመላለስንምን? በአንድ ፍለጋስ አልተመላለስንም?
19Vėl jūs manote, kad prieš jus teisinamės. Mes kalbame prieš Dievą Kristuje: viską darome, mylimieji, jūsų ugdymui.
19ለእናንተ ስለ ራሳችን እንድንመልስ ሁልጊዜ ይመስላችኋልን? በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን፤ ነገር ግን፥ ወዳጆች፥ እናንተን ልናንጻችሁ ሁሉን እንናገራለን።
20Mat bijau, kad atvykęs nerasčiau jūsų tokių, kokių nenoriu, ir kad pats nebūčiau toks, kokio jūs nenorite; kad nebūtų nesantaikos, pavydo, piktumo, barnių, šmeižtų, apkalbų, pasididžiavimo, netvarkos,
20ስመጣ፥ እንደምወደው ሳትሆኑ አገኛችሁ ይሆናል እኔም እንደምትወዱት ሳልሆን ታገኙኝ ይሆናል ብዬ እፈራለሁና፤ ምናልባት ክርክር ቅንዓትም ቁጣም አድመኝነትም ሐሜትም ማሾክሾክም ኩራትም ሁከትም ይሆናሉ፤
21kad, kai vėl atvyksiu, Dievas nepažemintų manęs prieš jus ir man netektų liūdėti dėl daugelio, kurie pirmiau buvo nusidėję ir dar neatgailavo dėl padarytų netyrumo, ištvirkavimo ir gašlumo darbų.
21እንደ ገና ስመጣ በእናንተ ዘንድ አምላኬ እንዲያዋርደኝ፥ አስቀድመውም ኃጢአት ከሠሩትና ስላደረጉት ርኵሰትና ዝሙት መዳራትም ንስሐ ካልገቡት ወገን ስለ ብዙዎች ምናልባት አዝናለሁ ብዬ እፈራለሁ።