1Jau trečią kartą keliauju pas jus. “Dviejų ar trijų liudytojų lūpomis bus patvirtintas kiekvienas žodis”.
1ወደ እናንተ ስመጣ ይህ ሦስተኛዬ ነው፤ ሁሉ ነገር በሁለትና በሦስት ምስክር አፍ ይጸናል።
2Jau sakiau anksčiau ir sakau, kaip ir antrąkart lankydamasis pas jus, ir, būdamas atstu, dabar rašau tiems, kurie anksčiau nusidėjo, ir visiems kitiems,jeigu atvyksiu vėl, būsiu negailestingas.
2ሁለተኛ በእናንተ ዘንድ በነበርሁ ጊዜ እንደ ተናገርሁ አሁንም ደግሞ በሩቅ ስሆን፥ ክርስቶስ በእኔ አድሮ እንዲናገር ማስረጃ ከፈለጋችሁ፥ እንደ ገና ብመጣ እንዳልራራላቸው አስቀድመው ኃጢአት ላደረጉት ለሌሎችም ሁሉ አስቀድሜ ብዬአለሁ፥ አስቀድሜም እላለሁ። ክርስቶስም ስለ እናንተ አይደክምም ነገር ግን በእናንተ ኃይለኛ ነው።
3Jūs reikalaujate įrodymo, kad manyje kalba Kristus, o Jis nėra silpnas prieš jus, bet galingas jumyse.
4በድካም ተሰቅሎአልና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ኃይል በሕይወት ይኖራል። እኛ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንደክማለንና፥ ነገር ግን ስለ እናንተ በሆነ በእግዚአብሔር ኃይል ከእርሱ ጋር በሕይወት እንኖራለን።
4Nors Jis buvo nukryžiuotas dėl silpnumo, bet dabar gyvas Dievo jėga. Nors mes irgi silpni Jame, bet jums gyvensime su Juo Dievo galybe.
5በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን?
5Patikrinkite patys save, ar esate tikėjime. Ištirkite save! Ar nepažįstate savęs ir nežinote, kad jumyse yra Jėzus Kristus, jeigu tik nesate atmestini?
6እኛ ግን የማንበቃ እንዳይደለን ልታውቁ ተስፋ አደርጋለሁ።
6Bet turiu vilties, kad jūs suprasite, jog mes nesame atmestini.
7ክፉ ነገርንም ከቶ እንዳታደርጉ ወደ እግዚአብሔር እንጸልያለን፤ እኛ የምንበቃ ሆነን እንገለጥ ዘንድ አይደለም ነገር ግን እኛ ምንም እንደማንበቃ ብንሆን፥ እናንተ መልካሙን ታደርጉ ዘንድ ነው።
7Aš meldžiu Dievą, kad jūs nedarytumėte nieko blogo,ne tam, kad pasirodytume tinkami, bet kad jūs darytumėte gera, o mes būtume tartum atmestini.
8ለእውነት እንጂ በእውነት ላይ ምንም ለማድረግ አንችልምና።
8Juk nieko negalime daryti prieš tiesą, bet tik už tiesą.
9እኛ ስንደክም እናንተም ኃይለኞች ስትሆኑ ደስ ብሎናልና፤ እናንተ ፍጹማን ትሆኑ ዘንድ ለዚህ ደግሞ እንጸልያለን።
9Mes džiaugiamės, kai esame silpni, o jūs stiprūs. Ir taip pat norime jūsų tobulumo.
10ስለዚህ ጌታ ለማፍረስ ያይደለ ለማነጽ እንደ ሰጠኝ ሥልጣን፥ ከእናንተ ጋር ሳለሁ በቁርጥ እንዳልሠራ በሩቅ ሆኜ ይህን እጽፋለሁ።
10Todėl, būdamas toli, tai rašau, kad atvykęs neturėčiau griežtai elgtis, naudodamas valdžią, kurią man Viešpats suteikė tam, kad ugdyčiau, o ne kad griaučiau.
11በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ደኅና ሁኑ። ፍጹማን ሁኑ፥ ምክሬን ስሙ፥ በአንድ ልብ ሁኑ፥ በሰላም ኑሩ፥ የፍቅርና የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል።
11Galiausiai, broliai, likite sveiki. Būkite tobuli, džiaukitės paguoda, būkite vienos minties, gyvenkite taikiai, ir meilės bei ramybės Dievas bus su jumis.
12በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ።
12Pasveikinkite vieni kitus šventu pabučiavimu.
13ቅዱሳን ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
13Jus sveikina visi šventieji. Viešpaties Jėzaus Kristaus malonė, Dievo meilė ir Šventosios Dvasios bendravimas tebūna su jumis visais! Amen.
14የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።